Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ

8.5K posts

Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ banner
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ

Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ

@AddisZeybe

Discover #Ethiopia’s exquisite urban culture, History, updated #news, and more.

ኢትዮጵያ شامل ہوئے Mart 2018
38 فالونگ27.4K فالوورز
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ ری ٹویٹ کیا
Judd Devermont
Judd Devermont@JDevermont·
On this day in 1963, President Kennedy hosted Ethiopian Emperor Haile Selassie. Kennedy praised the Emperor's "memorable and distinctive appearance before the League of Nations in the mid-thirties which so stirred the conscience of the world."
Judd Devermont tweet media
English
27
189
547
65.2K
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
የመንግሥት ኃይሎች በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጽሙት የጅምላ ግድያና የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ እንዲቆም ሲሉ አምስት ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጠየቁ መስከረም 10፤ 2016 ዓ.ም. (አዲስ ዘይቤ፤አዲስ አበባ) አምስት የተፎካካሪ ፓርቲዎች ዛሬ ባወጡት ወቅታዊ መግለጫ በዘመነ ኢሕአዴግ ለተፈጠሩ ስህተቶች ሁሉ ይቅርታ ጠይቆ መንበረ ስልጣኑን የተቆጣጠረው የብልጽግና ፓርቲ የኢትዮጵያን ሕዝብ እምነትና ተስፋ አምክኗል ሲሉ አስታወቁ። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ፓርቲ፣ እናት ፓርቲ፣ ዐማራ ግዮናዊ ንቅናቄ እና አንድ ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ በጋራ መግለጫቸው የመንግሥት ኃይሎች በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጽሙት የጅምላ ግድያና የድሮን ጥቃት በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀዋል። ፓርቲዎቹ በመግለጫቸው አሁንም ብቸኛዉ መንገድ “ዉይይትና ድርድር” በመሆኑ መንግስት ግንባር ቀደም ኃላፊነቱን በመወጣት የድርድር ጥያቄ እንዲያቀርብ፣ የመንግሥት ኃይሎች ከሰፈሩባቸዉ የመደበኛና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአስቸኳይ እንዲለቁ ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ አክለውም ባልታወቁ ሥፍራዎች በጅምላ ማጎሪያዎች የታሰሩ ዜጎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣ ተዋጊ ኃይሎች ዓለም አቀፍ የጦር ሕጎችንና ይህንኑ የሚደነግገውን የጄኔቫ ስምምነት እንዲጠብቁ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት ግጭቶች በድርድር እንዲፈቱ ጫና ማድረግ አለባቸው ሲሉ ፓርቲዎቹ በሰጡት መግለጫ አሳስበዋል። አሁን በስልጣን ላይ ያለው የብልፅግና ፓርቲ የመፍትሔ ሀሳቦች ቸል በማለት ችግሮችን በኃይል አማራጭ ለመፍታት በሚያደርገው ሙከራ በሀገር ላይ ለሚደርሰው የከፋ ጉዳት በታሪክም፣ በሞራልም በሕግም ተጠያቂ ይሆናል ብለዋል። ሙሉ መግለጫው ከታች ተያይዟል።
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet mediaAddis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
AM
10
31
57
9.4K
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
📻 የጦር እና በሰብዓዊነት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች እንዳይመረመሩ የኢትዮጵያ መንግስት ጫና እያደረገ መሆኑን ተመድ አስታወቀ ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ:👇am.addiszeybe.com/featured/addis…
AM
0
28
43
4K
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬስ በ'ዘላቂ የልማት ግቦች'  ከተያዙ እቅዶች እስካሁን 15 በመቶ የሚሆነው ብቻ መሳካቱን ገልፀው ግጭቶች፣ ረሀብ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥ ፈተናዎች አሁንም ችላ መባላቸውን አሳስበዋል። ሙሉ ዘጋባውን ያንብቡam.addiszeybe.com/featured/addis…
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
AM
0
0
2
1.2K
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
💐እንኳን ለ 2016 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! 🌻🌼 🌼መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ🌻
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
AM
0
0
2
696
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
The G20 Member countries have agreed to grant permanent membership status to the African Union, recognizing the need to make the group more representative and inclusive of the global community.
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
English
0
2
6
1.7K
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
🎤 የአማራ ክልል አደረጃጀት አዲስ መዋቀርን ተከትሎ በርዕሰ መስተዳደሩ የተሾሙ አዳዲስ የዞን ዋና እና ምክትል አስተዳዳሪዎች
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
AM
1
0
0
698
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
🚫 አጎአን ጨምሮ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ የጣለውን ማዕቀብ ለአንድ ዓመት አራዘመ። የአሜሪካ መንግስት በትግራዩ ጦርነት ሳቢያ በኢትዮጵያ የጣለችው ማዕቀብ አሁንም አሳሳቢ የደህንነት ሁኔታዎች በመኖራቸው ለቀጣይ አንድ ዓመት እንዲራዘም ፕሬዝዳንት ባይደን ወሰኑ። የአዲስ ዘይቤ ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ am.addiszeybe.com/addis-ababa/Th…
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
AM
11
16
55
15.5K
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
በመቀሌ የተቃውሞ ሰልፍ ከ120 በላይ ሰዎች ሲታሰሩ በርካቶች በፖሊስ እንደተደበድቡ እና የታሰሩት የሶስቱ ፓርቲዎች ሊቃነመናብርት ካደሩብት ተወስደው የደረሱበት አልታወቀም ተብሏል። የአዲስ ዘይቤ ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ am.addiszeybe.com/featured/addis…...
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
AM
0
1
4
670
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
Exciting news: An Ethiopian-born cognitive scientist, Abeba Birhane, @Abebab is being recognized as one of TIME's 100 most influential individuals in artificial intelligence for her groundbreaking work in auditing datasets. Her efforts are bringing much-needed transparency and accountability to the industry. #AI
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet mediaAddis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
English
0
5
18
1.8K
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
የሐረሪ ክልል ፖሊስ በከተማው የደረሰውን የእሳት አደጋ መነሻና ኪሳራ እያጣራሁ ነው አለ ጳጉሜን 2፤ 2015 ዓ.ም. (አዲስ ዘይቤ፤ አዲስ አበባ) በሐረሪ ክልል በተለምዶ ሸዋበር ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ለጳግሜ 2 ቀን 2015 ዓ.ም አጥቢያ ከለሊቱ 10:00 ሰአት ገደማ ሸዋበር የሸቀጣሸቀጥ መደብር በተባለ ስፍራ እስካሁን "ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ" የእሳት አደጋ ደርሷል። አደጋው ወደ ሌላ አካባቢ እንዳይዛመት መደረግ ተችሏል ያለው የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን "ከአደጋው ጋር በተገናኘ መንስኤውን እና የወደመውን ንብረት ግምት" ፖሊስ እያጣራ ይገኛል ብሏል። የምርመራው ውጤት ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
AM
0
0
0
555
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
የዓረና ፓርቲ ሊቀ መንበር ዓምዶም ገብረስላሴን ጨምሮ ዛሬ ብቻ ከ20 በላይ ሰዎች ታሰሩ ጳጉሜን 2፤ 2015 ዓ.ም. (አዲስ ዘይቤ፤ አዲስ አበባ) በትግራይ ክልል 'ጥምረት ለስር ነቀል ለውጥ” በሚል የተሰባሰቡ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በዛሬ እለት ከጠሩት ሠላማዊ ሰልፍ ጋር ተያይዞ ከጠዋት ጀምሮ ይህ ዘገባ እስከወጣበት ሰዓት ድረስ ቢያንስ ከ20 የሚበልጡ ሰዎች ታስረዋል ተባለ። የሠልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እና የውድብ ናፃነት ትግራይ (ውናት) ምክትል ሊቀ መንበር አለምሰገድ አረጋይ ለአዲስ ዘይቤ እንደገለፁት “ሰልፉን የሚያስተባብሩ ከተፎካካሪ ፓርቲዎቹ የተውጣጡ የኮሚቴ አባላቶች በሙሉ ከሁለት አስተባባሪዎች በስተቀር ታስረዋል”። እንደ መረጃ ምንጮቹ ከሆነ ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ብቻ ከፖለቲካ ፓርቲዎች አመራርና አባላት ብቻ ዓምዶምን ጨምሮ 13 ሰዎች የታሰሩ ሲሆን፣ ስድስት የቀድሞ የትግራይ ሠራዊት (ቲዲኤፍ) ሰዎች፣ አራት ለሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ንፁሃን ሰዎች በአጠቃላይ ከ20 በላይ ሰዎች ለእስር ተዳርገዋል። ሰላማዊ ሰልፉ የተጠራበት ሮማናት አደባባይ አካባቢ “ከሰልፈኞች ቁጥር ያለተናነሰ የፀጥታ ኃይል” መኖሩ የተገለፀ ሲሆን አሁንም በሰልፈኞች እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግብግቡ እንደቀጠለም ተገልጿል።
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ tweet media
AM
0
1
5
1.5K
Addis Zeybe - አዲስ ዘይቤ
#updates የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮቹ በድጋሜ ታስረው ወደ ቀዳማይ ወያነ ማረሚያ ቤት ተወሰዱ በትግራይ ክልል ከነገ ጀምሮ በተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ሳቢያ ዛሬ ረፋድ ላይ ታስረው ከሰዓታት እስር በኋላ የተፈቱት የሳልሳይ ወያነ ሊቀ መንበር ሃያሉ ጎዲፋይ፣ የውድብ ናፅነት ትግራይ ሊቀ መንበር ዶ/ር ደጀን በርሀ እንዲሁም የባይቶና ዓባይ ትግራይ አመራር አቶ ክብሮም በርሀ  በድጋሜ መታሰራቸውን የአዲስ ዘይቤ ምንጮች ገለፁ።
AM
2
2
6
3.7K