
በ ዘርይሁን ገሠሠ
:
፧
<< እኤአ 1920 ታላቁ የነፃነት ታጋይ ማህተማ ጋንዲ ህዝቡ ቅኝ ገዢዎቹ እንግሊዞች ያሰናዱትን ቅኝ ግዛትን የማንበሪያ ምርጫ እንዳይሳተፍ ጥሪ አቀረቡ። ይህ ሰላማዊ ትግል በህንድ ውስጥ ታላቅ የሆነ የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ትግል እንዲፋፋም መነሻ ሆኗል።
በ2008 በዝምባዋብዌ የሮበርት ሙጋቤ ተፎካካሪ የነበሩት ሞርጋን ቫንግራይ - የሙጋቤ አገዛዝ ካሰናዳው አገዛዝን የማስቀጠል ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ራሳቸውን አገለሉ። በዚህም ሙጋቤ የይስሙላ ምርጫውን እንደተለመደው ''አሸነፍኩ'' ብለው ቢያውጁም በዜጎቻቸው ያላቸው ቅቡልነት ገደል ገባ። አለምአቀፋዊ ውግዘትና ጫናን አስተናገዱ። በመጨረሻም ሙጋቤ ሳይወዱ ተገደው ተቃዋሚዎች በሀገሪቱ መንግስት ድርሻ እንዲኖራቸው ተደራደሩ።
በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ አገዛዝ ወቅት - አገዛዙ ጥቁሮችን ሙሉ በሙሉ ያገለለ ፣ ህንዶችንና ከነጮች ጋር ድብልቅ የዘር ሀረግ ያላቸውን በአንድ ምድብ ያካተተ የፓርላሜንት ( Tricameral Parliament ) ስርአት በመፍጠር August በ1984 ያካሄደውን ምርጫ ፣ አብዛሀኞቹ ህንዳውያንና ድብልቅ ዘር ያላቸው መራጮች በምርጫው ቀን ባለመሳተፍና ከቤታቸው በመቀመጥ ተቃውሟቸውን ጀመሩ።
51% የሚሆነው መራጭ ድምፁን ባለመስጠት ለፕሬዝደንት P.W. Botha ሪፎርም እንዲያደርጉ እጃቸውን የጠመዘዘ ግልፅ መልዕክት አስተላለፉ። 50% የአፓርታይድ ትግሉ ድል የተቀዳጀው በዚህ ታሪካዊና ሰላማዊ ትግል መሆኑም በታሪክ ይወሳል።
በሰርቢያ (1997) ፣ በቬኔዙዌላ (2018) ፤ ባንግላዴሽ (2014) ፤ ....ወዘተ የተደረጉ ሰላማዊ የአንባገነኖችን የይስሙላ ምርጫ ያለመሳተፍ ( boycotting Election ) ትግሎች ያስመዘገቧቸውን ውጤቶችና ሀገራዊ ለውጦች መመልከት ይቻላል። ...... >>
#boycott_Election_2018
AM















