News

7.5K posts

News banner
News

News

@NISIRInternati1

United States; Africa; Europe Katılım Ocak 2021
46 Takip Edilen7.3K Takipçiler
News
News@NISIRInternati1·
እነኳን ለ2018 ዓ.ም አደረሳችሁ! ************** *የአማራ ህዝብ ዋስትና ለሆንከው ለመላው የአማራ ፋኖ! *በየ እስር ቤቱ ታጉራችሁ በስቃይ ለምትገኙ የአማራ ልጆች! *ለአማራ ፋኖ ወላጆችና የታጋይ ቤተሰቦች! *ለመላው የአማራ ትግል ደጋፊወችና ኢትዮጵያውያን በሙሉ! እንኳን ለ2018 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! አዲሱ አመት የአማራ ህዝብ ትግል በድል የሚጠናቀቅበት እንዲሆን እንመኛለን። እንደሚታወቀው የአማራ ህዝብ ለአመታት በጦርነት ቀንበር ውስጥ ሆኖ ኑሮውን እየገፋ ይገኛል። ንሥር ብሮድካስት ኮርፖሬሽንም በአማራ ህዝብ ላይ የተፈፀመውን እና እየተፈፀ ያለውን ጥቃት አስመልክቶ አማራው እራሱን እንዲያነቃና እራሱን ከጥቃት መከላከል እንዲችል ከ2013 ዓ. ም ጀምሮ ላለፍት አመታት እለታዊ መረጃወችን በየቀኑ በማቅረብ አስተዋጽኦ ሲያደርግ ቆይቷል። ይህን አረመኔና አገር አጥፊ ስርዓት በማጋለጥና ወገናችን ላይ የሚፈፀመውን ጥቃት ለማስቆም በሚደረገው እርብርብ ንሥር ብሮድካስት የራሱን ሚና ተጫውቷል። ሆኖም ከ2018 ጀምሮ የእለታዊ ዜና ስርጭት ፕሮግራማችን ስለማይኖር እሰከ አሁን ስትከተሉን የነበራችሁ ተከታዮቻችንና እንዲሁም መረጃ ስታደርሱን የነበራችሁ ምንጮቻችንን ከልብ እያመሰገን ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ሌሎች ተመሳሳይ የትግል ሚዲያወችን እንድትጠቀሙና እንድትከተሉ በአክብሮት እናሳስባለን። ለወደፊትም ከድል በሗላ በሌሎች የአማራ ትግል ታሪክ ዶክመንታሪወች እና ለነፃነት የተዋደቁ ወገኖቻችን በሚዘክሩ ፕሮግራሞች ተመልሰን እንደምንገናኝ ለማስታወስ እንወዳለን። በመጨረሻም የተጀመረው የህልውና ትግል ከግብ እንዲደርስ እና በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ሁሉም አማራ እና የአማራ ትግል ደጋፊ በጋራ እንዲቆም፣ በአንድነትና በህብረት እንዲታገል እናሳስባለን። ድል ለጀግናው የአማራ ፋኖ! ድል ለአማራ ህዝብ! መልካም አዲስ ዓመት! ንሥር ብሮድካስት ኮርፖሬሽን ዕረቡ ዻጉሜ 5/2017 ዓ.ም
News tweet media
AM
0
0
10
1.2K
News
News@NISIRInternati1·
1/ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኀ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር ታድሎ ብርሃን ክ/ጦር ጅባስራ ብርጌድ እና ከጎንደሬ በጋሻው ፋሲለደስ ብርጌድ  ጳጉሜ 1/2017 ዓ.ም ጎንደር ዙሪያ ወረዳ ከባህሪ ግንብ እስከ ብርቧክስ እና አርሴማ ድረስ የሸፈነ ከጠላት ጋር ውጊያ በማድረግ በጠላት ላይ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት አድርሰውበታል።    ከ10 በላይ ሙትና ቁስለኛ የሆነው የብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ሸሽቶ ወደ ጎንደር ከተማ ገብቷል።     2/ በስርዓት አልበኞች ላይ ርምጃ መሰድ ተጀመረ! ከጎንደር ደባርቅ ዋና አውራ ጎዳና አሽከርካሪዎችንና መንገደኞችን በመዝረፍ የውንብድና ተግባር ተሰማርተው በነበሩ ወሮበሎች ላይ ዛሬ ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ ርምጃ መውሰድ ተጀምሯል። በተለይም ከአምባጊዮርጊስ ደባርቅ መስመሮች ላይ ሲዘርፉ፣ሲያግቱ እና የውንብድና እኩይ ድርጊት ለመፈፀም ተሰማርተው በነበሩ ስርዓት አልበኞች ላይ እየተወሰደ በሚገኘው የተጠና ኦፕሬሽን መስመሩን ለጊዜው ከወሮበሎች ማፅዳት የተቻለ ሲሆን በዘላቂነት ችግሩን ለመቅረፍ ጠላት በሰፈረባቸው አካባቢዎች ድረስ ዘልቆ ማፅዳት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል።     ተበትነው የተሰወሩ ወንበዴዎች እጅ እየሰጡ ሲሆን ህዝቡ እየተወሰደ ለሚገኘው ስርዓት የማስያዝ ርምጃ እየተሳተፈ ይገኛል። 3/ የአደረጃጀት መረጃ የ ዘራይ አዝመራው ክፍለ ጦር አዲስ ዓመትን”ውስጣዊ ችግር በመፍታት ሃይል እንገንባ!መሪ እንፍጠር” በሚል መሪቃል ለሁለት ዓመታት  በአርበኛ ኢንጅነር በየነ አለማው እና አርበኛ አስምሮ ፍቃዴ ሲመራ የቆየው ዘራይ ክፍለ ጦር ሙሉ ሪፎርም አድርጓል። አውናዊ የክፍለ ጦሩ ቁመና መደበኛ የብርጌድ ስታዳርድ ባሞሉ አምስት ብርጌዶች የተዋቀረ ነው። እነዚሁ ብርጌዶች፦ 1. ቆራጡ ገብሬ አቡሃይ ፩ኛ ብርጌድ 2. ሸጋው ውበት ፪ኛ ብርጌድ 3. ሃይሌ ማሞ ፫ኛ ብርጌድ 4. ንግስቷ ሰላም ጥላሁን ፬ኛ ብርጌድ 5. ሞላ ደጀን ማይካድራ ብርጌድ ሲሆኑ የዘራይ ክፍለ ጦር እንደሚከተለው ሁኖ ተዋቅሯል። 1. የዘራይ ክፍለ ጦር ሰብሳቢ-አርበኛ እሱባለው ይርጋ 2. ወታደራዊ አዛዥ-አርበኛ ፻ዓለቃ የሽበር አስማማው 3. ም/ል ወታደራዊ አዛዥ-አርበኛ አምሳሉ ዘሪሁን 4. ዘመቻ-አርበኛ ሙሉቀን ያለው 5. ም/ል ዘመቻ-አርበኛ አማኑኤል አጥናፉ 6. አስተዳደር-አርበኛ ፶ዓለቃ ትግስት ተረፈ 7. ሎጅስቲክ አስተዳደር-አርበኛ ጋሻው መሰለ 8. ልዩ ተልዕኮ-አርበኛ ገብሬ ሸቴ 9. ስለጠና-አርበኛ አሜሪካው አለባ 10. ኦርዲናስ-አርበኛ ይበልጣል ጌታቸው 11. ገንዘብ አስተዳደር-አርበኛ ጌታቸው ዘሪሁን 12. ፖለቲከ ዘርፍ-አርበኛ ላቀው ፈረደ 13. ህዝብ ግንኙነት-አርበኛ ፍቅሩ የማታው 14. መረጃ እና ደህንነት———- 15. ህዝባዊ አስተዳደር-አርበኛ ቃቀይ ጌትነት 16. ህግ እና ስነ-ምግባር-መምህር አስቻለው አግንቸ      በመሆን ዘራይ ክ/ጦር አመራር አዋቅሯል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !! አፋብኃ ምዕ/አማራ ቀጠና ቴወድሮስ እዝ ቃል አቀባይ ማርሸት ፀሃው ጳግሜ 4/2017/
AM
0
0
3
921
News
News@NISIRInternati1·
የአፋብኅ ምዕራብ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ ፫ኛ ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ እና ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ድማማ ማንጉዳ ላይ ተከማችቶ ከነበረዉ የአድማ ብተና ሚሊሻ እና የፖሊስ ታጣቂ ላይ በወሰደዱት በለሊት ጠላትን የማፅዳት ኦፕሬሽን ተሻለ ዳኘዉ የተባለን ከሀዲ ጨምሮ 9 የሚሆነዉን በመደምሰስ ከ12 በላዩን ቁስለኛ አድርገዉ 3 ክላሽንኮቭ 1 ሲሶ ክላሽ 1370 የክላሽ ተተኳሽ ተረክበዋል። በተደጋጋሚ በደረሰበት ምት የአረመኔው ሰራዊት ለፋኖ እጅ እየሰጠ ይገኛል ። ቢቸና ከተማ መሽጎ የሚገኘው የሚሊሻ ካንፕ በመክዳት ፋኖን ከተቀላቀሉት መካከል 1ኛ.ተሾመ ክብሬ አድራሻ ሸበል በረንታ ሌዲ ቀበሌ 2ኛ. ውድ አቡ ሸበል በረንታ ወቦ ወሬ ቀበሌ ተወላጅ የነበሩ 8ኛ በላይ ዘለቀ ክ/ጦር ሽፈራው ገርባው ብርጌድ ተቀላቅለዋል። በተመሳሳይ ቀረብህ ሲሳይ የተባለው ሚሊሻ ለቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ከፍለ ጦር ኢንጅነር ክበር ተመስገን ብርጌድ እጁን በሰላም ሰጥቷል። ሌሎቻችሁም የምሕረት ጥሪያችንን በመቀበል ራሳችሁን ከከንቱ መስዋዕትነት አድኑ ስንል መልዕክታችን ኦናስተላልፋለን። ከሕዝባችን ጋር የምናደርገው ውይይት በተጠናከረ መንገድ ቀጥሏል። የአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር የስናን አባጅሜ ብርጌድ ከሸዋ ኪዳነ ምሕረት ቀበሌ ማሕበረሰብ ጋር ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ የአማራ ትግል የደረሰበት የልዕልና ጥግ ለማሕበረሰቡ የተገለጸ ሲሆን በመልካም አስተዳደርና በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፋ ያለ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምሕርት ተሰጥቷል። ሕዝባችን የምንሞትለት የምንሰዋለት፣ ዝቅ ብለን የምናገለግለው በቀደመ የአርበኝነት ታሪኩ አንጸባራቂ ድል ሰርቶበት ለታሪክ ምስክር ያስቀመጠውን አልቬን፣ቤልጅግ፣ ምንሽር...መሳሪያውን አስታጥቆ በደሙ ላወረሰን ታሪኩ ፣ማንነቱ፣ ዕምነቱና ሕልውናው እንድንዋደቅ እስከ ደም ጠብታና እስከ ሕይወት መስዋዕትነት እንድንታገል ለዛና በረከት ባለው አንደበቱ ባርኮና መርቆ የሸኘን ነው። ሕዝባችን ጥላችን ሁሉ ነገራችን ነው። ሕዝባችን ቀይ መስመራችን ነው። አዲስ ትውልድ ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ! አፋብኃ| ቴዎድሮስ ዕዝ ጳጒሜ 03/2017ዓ.ም
News tweet media
AM
0
2
11
1.4K
News
News@NISIRInternati1·
በአዲሱ ዓመት አማራነትን ፀረ-አማራነት ከማይደርስበት ሰገነት እናስቀምጠዋለን ! ምላጭ የመዋጥ ያክል ከብዶ የነበረው አማራዊ አንድነት በአንድ ማንኪያ ቅንነት ጥሩ የአዲስ አመት ዋዜማ ላይ እንድንገኝ አድርጎናል ። ይሔ አማራዊ አንድነት በፍጥነት እየተጎዘ በሚሄድበት ወቅት ከሚፈለገው ቦታ ለመድረስ በአንድነት ጉዞ ውስጥ የሚገኙ መንገደኞች የኋላ እና የፊት መስታውት በመመልከት ፣ አቅጣጫ በመጠቆም ፣ መስታውት በመወልወል ወይም ፀሎት በማድረግ ማገዝ አማራዊ ግዴታው ነው ። ነገር ግን የባሱን መሪ ፣ ፍሬን እና ነዳጅ መቆጣጠሪያውን ለሹፌሩ መተው ደግሞ ጉዞውን ሙሉ ጤነኛ እንዲሆን ያደርጋዋል። በዚህ ጉዞ ላይ ለተሳፋሪዎችም ሆነ ለሹፌሩ ሳይናገር ለመውረድ የሚሞክር ካለ ግን ፈጣሪ ፣ ህዝብ ፣ጊዜ እና ታሪክ የትውልዱ መሣቂያ እና መሣለቂያ ያደርጉታል ። የአማራነት ሰይፍም ይበላዋል ። የድንጋይ ዘመን አስተሳሰብ ባለቤቶች አማራነትን በብዙ ሰው ሰራሽ እና ስርዓት መር ችግሮች ከቀበሩበት የብረት በርሚል ውስጥ አዲሱ ትውልድ ከቀበሩበት አውጥቶ ለዓለም ህዝብ እያሣየው ይገኛል ። ከዚህ ስንደርስ ግን እልፍ አይተኬ የጀግኖች ህይወትን ገብረንበት፣ እልፎች አካለ ጎደሎ ሁነውበት፣ እልፎች ወሕኒ ቤት ታጉረውበት፣ እልፎች ሀብት ንብረታቸውን አጠው በስደት አገር ሰሪ አገር አልባ ሁነውበታል ። በነዚህ አስቸጋሪ የአማራው ዓመታቶች ፈጣሪ ፣ ታሪክ ፣ ጊዜ እና ህዝብ በደንብ እየታዘቡን ወየም እየመዘኑን ይገኛሉ ። ከአራቱ ሚዛኖች በአንዱ ተመዝኖ የወደቀ ሰው ደግሞ በፍፁም ዋጋ የማያወጣበት ወድቆ የማይነሳበት ደረጃ ላይ ይደርሳል ። ምንም አይነት ሰዋዊ ልዩነቶች ቢኖሩብንም እንኳን እንደ ህዝብ ላለመጥፋት ቤት ንብረታችን ጥለን የወጣን የአማራ ልጆች አንድ ለመሆን የሚያስቸግረን ጉዳይ ይኖራል ተብሎ አይገመትም ። ወቅቱ ምንም በዓይንህ ማየት ማትፈልገው ሰው እንኳን ቢሆን ለህዝባችን አንድነት ሲባል ቀድመህ ይቅርታ ጠይቀህ ወደ ስራ ምትገባበት ጊዜ ነው ። በነፃ ለነፃነት የሚታገል ታጋይ እና አታጋይ ትልቁ ደሞዙ ' ነፃነት ' ነው ። ነፃነት ደግሞ በነፃ አይገኝም ። ነፃነት ጨርሶ የሚያጠፋ ወይም የሚያም 'ዱላ' አለው ። ዱላው የወንድም ከሆነ ደግሞ ቢያምም ያድናል ። አማራነት ወደ ባለቤቱ የአማራ ህዝብ እንዲመለስ ደግሞ አዲሱ ትውልድ አንድ አማራ እና አንድ የጥይት ፍሬ እስክትቀረው ድረስ ታግሎ ያስከብረዋል ። አማራነትን ፀረ አማራነት ከማይደርስበት ሰገነት ከፍ አድርጎ ያስቀምጠዋል ። አማራነትን ባለቤቱ ብቻ ሊያውቀው በሚችለው መፍቻ ተቆልፎ ይቀመጣል ። ምክንያቱም አማራነት የባለቤቱ ውድ ንብረት ስለሆነ እና በአደራ ለሌሎች የማይሰጥ ማንነት ስለሆነ ። ፈጣሪ ሁሌም ጥሩ ዘመኖችን ሲሰጠን ቆይቷል ። እነዚያን ዘመናቶች ጥሩ ወይም መጥፎ ምናደርጋቸው እኛው የእርሱ ፍጥረቶች ነን ። አሁን ግን ፈጣሪ ጥሩ ዘመን ብቻ አይደለም የሠጠን ጥሩ መሪ እና መልካም አጋጣሚዎችን ፈጥሮልናል ። የተሠጡንን መልካም አጋጣሚዎች ለአማራው እና ለፍትሕ ወዳድ ሀገሬው የሚበጅ አድርጎ መጠቀም ወይም መስራት ደግሞ የዚህ ትውልድ ለነገ የማይባል አሁናዊ ስራው ተደርጎ መታወጅ አለበት ። ይሔን ጊዜ እና መልካም አጋጣሚ በአግባቡ ሳንጠቀም ከቀረነ እና እንደ ህዝብ ካልጠፋነ ሌላ 500 ዓመት ከመከራ እና ጭቆና ጋር ለመጠበቅ እንገደዳለን ። እኛ ደግሞ ይህ እንዲሆን የማንፈልግ ትውልዶች ነን ። በጳጉሜ ውሐ መንፃት ለሠውነታችን እና ለልብሶቻችን ብቻ ሳይሆን ለአስተሳሰባችንም ስለሚጠቅም በደንብ እንጠቀምበት ። ' እጅ ከለቀቀ ብልሐት አለቀ ' የሚለው የሕፃናት የብይ ጨዋታ ህግ ለአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ አሰላለፍም ይሰራል ። እጃችን ላይ ያለውን መልካም አጋጣሚ ሁሉ በማስተዋል መጠቀም ለነገ ቤታችን ማማር ትልቅ ጉልበት ስለሚኖረው ለመጠቀም ግዴለሽ መሆን አያስፈልግም ። ሰገነቱ ላይ እንገናኝ ! መልካም ዓዲስ ዓመት ! አዲስ ትውልድ ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣ አዲስ ተስፋ ! አርበኛ ግሩም ምሳሌ
AM
1
1
8
980
News
News@NISIRInternati1·
መልካም ዜና! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የኮር ምስረታ አካሄደ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ አምስት ክ/ጦሮችን ወደ አንድ በማሰባሰብ ግዙፉን የፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር አንድ መስርቷል:: ይህንን ኮር አፄይኩኖ አምላክ፥ ሰባት ለሰባ፥ ነጎድጓድ፥ ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክ/ጦሮች በአንድ ላይ ሁነው ነው የመሰረቱት :: ይህ የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር ምስረታ ሥነ ስርዓት የአሳምነው እዝ አመራሮች፥ የየክ/ጦር መሪዎች፥ የፋኖ አባላት፥ አባት አርበኞች፥ የሀይማኖት አባቶች፥ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በኤፍራታና ግድም ወረዳ በደራሲና አርበኛ አሰገድ መኮነን መቀመጫ ማጀቴ ተካሄዷል:: በዚህ የኮር ምስረታ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው እዝ አፄ ይኩኖ አምላክ፥ ሰባት ለሰባ ፥ነጎድጓድ ፥ ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክ/ጦር የፋኖ አባላት በወታደራዊ ሰልፍ ተመው በመምጣት ተሳታፊ ሁነዋል:: የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር ምስረታ ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድ አባል እና ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ዋና መሪ አርበኛ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ እስካሁን የገጠሙንን በርካታ ተግዳሮቶች በፋኖ አርበኞቻችን እና በማህበረሰባችን ጥንካሬ ተወጥተን የጋራ መሰባሰቢያ ቤታችንን ከሸንኮራ እስከ ቋራ ተጉዘን ገንብተን በመጣን ማግስት ታላቁን የፄ ዘርያይቆብ ኮር መመስረት መቻላችን ጥንካሬያችን የታየበት በመሆኑ ሁላችንም ደስ ሊለን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል:: በኮር ምስረታው የተገኙት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ሴንትራል ኮማንድ አባል እና የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ዋና ወታደራዊ አዛዥ ፊት አውራሪ ድርሳን ብረሀኔ ከአሳምነው ዕዝ ጋር በጋራ በመስራት የጥላትን ቅስም የምንሰብርበት ወቅት ሩቅ አይደለም ብለዋል:: ይህንን የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ አንደኛ ኮር ምስረታ በተመለከተ የስም ስያሜ በአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የድርጅት ጉዳዮች ኃላፊ አርበኛ አሸናፊ ምንዳ በኩል ማብራሪያ ተሰጥቶ የዕዙ የድርጅት ጉዳዮች  የቀጣይ እቅድ የሚያመላክቱ መልእክቶች ተላልፈዋል:: በዚህ የኮር ምስረታ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ዋና አዛዥ ፊት አውራሪ ባዩ አለባቸው የፋኖ ኃይል ሊከተላቸው የሚገቡ የቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችና ወታደራዊ መመሪያ ምን መምሰል እንዳለባቸው መልእክት አስተላልፈዋል:: የኮር ምስረታ ፕሮግራሙም በተለያዩ መጣጥፎች፥ ግጥሞች፥ ሽለላና ቀረርቶ በድምቀት ከተካሄደ በኋላ  የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል እንዲመሰረት ከሸንኮራ እስከ ቋራ ተራራ ሸንተረሩ ቁርና ብርዱ እንዲሁም የጠላት ሀይል ሳይበግራቸው አንድ የአማራ ቤት ሰርተው ለተመለሱት የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች የቃል ኪዳን ምልክት የሆነችውን የአባቶቻችን የቃል ኪዳን አርማ የሆነችውን ሰንደቅ ዓላማ በማበርከት ለቀጣይ መሪነት ዝግጁ እንዲሆኑ ተደርጓል:: በመጨረሻም የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ም/ል መሪ በአርበኛ ኢሳያስ ደመቀ የአፄ ዘርአያዕቆብ ኮር አንድ መሪ ሁነው የተመደቡ የፋኖ አመራሮች ቃለመሀላ እንዲፈጽሙ ተደርጎ የተመደቡ አመራሮች የአማራ ህዝብ የጣለባቸውን አደራ በብቃት እንዲወጡ ጭምር መልእክት በማስተላለፍ እና ከብልጽግና ጋር ወግነው ለሚሰሩ አመራሮች፥ የአድማ ብተና ፥የሚኒሻ ፥ እና የመከላከያ አባላት የፋኖን ትግል እንዲደግፉ ጥሪ በማስተላለፍ ፕሮግራሙ ተጠናቋል:: የኮሩን አመራሮች ዝርዝር ሙሉ መረጃ እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።    "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን" አፋብኃ ደቡብ  አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝየህዝብ ግንኙነት ዜና ክፍል        ጳጉሜ 03/2017 ዓ.ም
AM
0
1
3
543
News
News@NISIRInternati1·
የአረመኔ ስርዓት ጦር እየፈረሰ ነው አፋብኃ የምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 5ኛ ክፍለ ጦር ወርቅ አባይ ብርጌድን የአረመኔው ስርዓት ወንበር ጠባቂ የነበሩ የመከላከያ ወታደሮች ቀን በቀን እየፈረሱ ወርቅ አባይን ተቀላቀሉ።ስርዓቱን ሲያገለግሉ እና ሲታገሉ የነበሩ ወታደሮች በአማራ ህዝብ ላይ የመከላከያ ሰራዊቱ  የሚፈፀመው ግፍ እና ሰቆቃ መቋቋም ስላቃተን ነው የወጣነው በማለት ሁለት የመከላከያ ወታደሮች ሁለት ጥቁር ክላሽ ይዘው ከእነ ሙሉ ትጥቃችን ፋኖን የተቀላቀልን ብለዋል። አገዛዙ በድጉ እና በሰፊው ህዝብ ላይ እየፈጸመው ያለው ጅምላ ጭፍጨፋ እና ማንነትን ተኮር ያደረግ  በመዝረፍ እና ቤታቸውን በማቃጠል ከሚኖሩበት አካባቢ መፈናቀል፣መግደል እና ሴቶችን መድፈር የተሰጠን ተልዕኮ ቢሆንም ለአማራ ህዝብ የማይገባ መሆኑን ስለተረዳን ከአገዛዙ ከድተን ፋኖን ተቀላቅለናል ሲሉ የኦሮሚያ ተወላጅ የሆኑት ወ/ር ካሱ ወልዱ እና ጋዲሳ መገርሳ ተናግረዋል። ንጹሃን አርሷደሮችን ከቤት እያወጡ እና የቀን ሰራተኞቹን በግፍ እና በሰቆቃ እረሽነዋል አስረዋል። እንዲሁም በእሁዲት ከተማ በማህበረሰቡ ላይ የፈጸሙት በድል ለአማራ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ህዝብም ጥቁር ታሪክ ሁኖ የሚቀመጥ ይሆናልም በለው አክለው ገልጸዋል።ጠላትን ስቦ በማስከዳት እና በመደምሰስ አፋብኃ የምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 5ኛ ክፍለ ጦር አጠናክሮ ቀጥሎበታል። ፲/አ እ/ር ዘመኑ አማረ 5ኛ ክ/ጦር ህ/ግ መምሪያ ኃላፊ ጳግሜ 3/2017/
AM
0
0
3
492
News
News@NISIRInternati1·
የፋኖ ቤተሰቦችን ያነጣጠረ ጥቃት ተፈፀመ በአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ 2ኛ /ተፈራ ዳምጤ/ ክፍለ ጦር  መዝገበ ጮቄ ብርጌድ  በደብረ ሰላም ቀበሌ ኑዋሪ በሆኑት አቶ ጌትነት እንየው ላይ ሰዴ ከተማ  ቤተ-ክርስቲያን በሄዱበት ፋኖ ልጅ አለህ በማለት በዚህ መልኩ ተደብድበው ህክምና ላይ ይገኛል ። አቶ ጌትነት እንየው የ72  ዓመት ሽማግሌ ሲሆኑ በግብርና የሚተዳደሩና  አርሶ ከማደር ውጭ ወቅታዊ  የፖለቲካ ሁኔታ እንኳን በቅጡ  ለይተው የማይረዱ በርካታ ቤተሰብ በመምራትና  ታዋቂ የሀገር  ሽማግሌ የሆኑ ምስጉን አርሶ አደር ናቸው።ነገር ግን አማራ ከመሆናቸውና በተጨማሪ  ታደለ ጌትነት የሚባል ልጃቸው  መዝገበ ጮቄ ብርጌድ ውስጥ የአማራን ህዝብ ከመጥፋት ለመታደግ እንደ ሁሉም አማራ ወጣት እየታገለ ስለሚገኝ ለመደብደባቸው ትልቁ ምክንያት መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል ። የአቶ ጌትነት እንየው የመኖሪያ ቤት ለከተማው ቅርብ በመሆኑ የተወሰኑ የሚኒሻ አባላት ወደ ቤት በመሄድ የቦንብ ጥቃት ለማድረስ ሙከራ ቢያደርጉም የመዝገበ ጮቄ ብርጌድ ሻለቃ ሶስት መረጃ ስለደረሳት ተከታትላ ጥቃቱን በማክሸፍ ጥቃት አድራሾችን ወደ መጡበት በማባረር መልሳለች ። ከዚህ በፊት በርካታ ጊዜ የፋኖ ቤተሰቦችን ማሰር፣ ማንገላታት ፣ መግረፍ እንዲሁም ከማዳበሪያና  ምርጥ ዘር እንዲሁም ከየትኛም የማህበረሰብ አግልግሎት  ውጭ  በማድረግ እንደ አማራ ህዝብ ከሚደርሰው ግፍ በተጨማሪ የተለየ ጭቆናና አፈና ሲፈፀም ቆይቷል። ሁኖም ግን በፋኖ በኩል በሆደ ሰፊነትና  በአስተዋይነት ከሚገባው በላይ ትግስትን ተላብሰን ሆድ አደር ሚኒሻና የብልፅግና አመራር  በእኛ ቤተሰቦች ላይ የሚያደርሰውን በእነሱ ላይ ከማድረግ ተቆጠበን ቀይተናል ። ከዚህ በኋላ ግን ለየትኛውም ቤተሰቦቻችን ላይ ለሚደርስ ጥቃት ትይዩ ዕርምጃ የምንወስድ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን ። በመጨረሻም የተከበራችሁና የተወደዳችሁ የባንዳ ቤተሰቦች ይህንን አስነዋሪ ድርጅት የሚሰሩ የቅርብ ቤተሰቦቻችሁን ጥብቅ ምክርና ማሳሰቢያ እንድትሰጡ ከወዲሁ እናሳስባለን። መዝገበ ጮቄ ብርጌድ ጳግሜ 3/2017/
AM
0
0
3
390
News
News@NISIRInternati1·
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ "የፖለቲካ መኮንኖችን" በድምቀት አስመረቀ:: የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ "ፀሃፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሃብተወልድ የፖለቲካ መኮንን ማሰለጠኛ ማዕከል" የሚል ፕሮጀክት በማቋቋም የመጀመሪያ ዙር የፖለቲካ መኮንኖችን ለበርካታ ቀናት ሲያሰለጥን ቆይቶ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድምቀት አስመርቋል። የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ የፖለቲካ ዘርፍ ሥር የተቋቋመው የፖለቲካ መኮንኖች ማሰልጠኛ ማዕከል በኢትዮጵያ የፖለቲካና የድፕሎማት ታሪክ ደማቅ አሻራ ባለቤት በሆነው ፀሃፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሃብተወልድ ስም በመታሰቢያነት ተሰይሟል። ከሁሉም ኮሮች የተመለመሉ ሰልጣኝ የፖለቲካ መኮንኖች በርካታ ዉጣዉረዶችን አልፈው ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለምረቃ በመብቃታቸው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች የተላለፈ ሲሆን የመኮንን ተመራቂዎቹ በሰለጠኑት መሰረት በአማራ ብሔርተኝነት መስመር ትግሉን በትጋትና በንቃት ለማገልገል፣ ድርጅታችን አፋብኃን ለመጠበቅ፣ ፖለቲካዊ ሥራዎችን ለመስራት ቃል ገብተዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ጳጉሜ 3/2017 ዓ.ም
News tweet mediaNews tweet media
AM
0
5
22
1.2K
News
News@NISIRInternati1·
መልካም ዜና! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የኮር ምስረታ አካሄደ ================ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ አምስት ክ/ጦሮችን ወደ አንድ በማሰባሰብ ግዙፉን የፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር አንድ መስርቷል:: ይህንን ኮር አፄይኩኖ አምላክ፥ ሰባት ለሰባ፥ ነጎድጓድ፥ ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክ/ጦሮች በአንድ ላይ ሁነው ነው የመሰረቱት :: ይህ የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር ምስረታ ሥነ ስርዓት የአሳምነው እዝ አመራሮች፥ የየክ/ጦር መሪዎች፥ የፋኖ አባላት፥ አባት አርበኞች፥ የሀይማኖት አባቶች፥ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በኤፍራታና ግድም ወረዳ በደራሲና አርበኛ አሰገድ መኮነን መቀመጫ ማጀቴ ተካሄዷል:: በዚህ የኮር ምስረታ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው እዝ አፄ ይኩኖ አምላክ፥ ሰባት ለሰባ ፥ነጎድጓድ ፥ ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክ/ጦር የፋኖ አባላት በወታደራዊ ሰልፍ ተመው በመምጣት ተሳታፊ ሁነዋል:: የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር ምስረታ ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድ አባል እና ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ዋና መሪ አርበኛ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ እስካሁን የገጠሙንን በርካታ ተግዳሮቶች በፋኖ አርበኞቻችን እና በማህበረሰባችን ጥንካሬ ተወጥተን የጋራ መሰባሰቢያ ቤታችንን ከሸንኮራ እስከ ቋራ ተጉዘን ገንብተን በመጣን ማግስት ታላቁን የፄ ዘርያይቆብ ኮር መመስረት መቻላችን ጥንካሬያችን የታየበት በመሆኑ ሁላችንም ደስ ሊለን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል:: በኮር ምስረታው የተገኙት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ሴንትራል ኮማንድ አባል እና የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ዋና ወታደራዊ አዛዥ ፊት አውራሪ ድርሳን ብረሀኔ ከአሳምነው ዕዝ ጋር በጋራ በመስራት የጥላትን ቅስም የምንሰብርበት ወቅት ሩቅ አይደለም ብለዋል:: ይህንን የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ አንደኛ ኮር ምስረታ በተመለከተ የስም ስያሜ በአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የድርጅት ጉዳዮች ኃላፊ አርበኛ አሸናፊ ምንዳ በኩል ማብራሪያ ተሰጥቶ የዕዙ የድርጅት ጉዳዮች  የቀጣይ እቅድ የሚያመላክቱ መልእክቶች ተላልፈዋል:: በዚህ የኮር ምስረታ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ዋና አዛዥ ፊት አውራሪ ባዩ አለባቸው የፋኖ ኃይል ሊከተላቸው የሚገቡ የቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችና ወታደራዊ መመሪያ ምን መምሰል እንዳለባቸው መልእክት አስተላልፈዋል:: የኮር ምስረታ ፕሮግራሙም በተለያዩ መጣጥፎች፥ ግጥሞች፥ ሽለላና ቀረርቶ በድምቀት ከተካሄደ በኋላ  የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል እንዲመሰረት ከሸንኮራ እስከ ቋራ ተራራ ሸንተረሩ ቁርና ብርዱ እንዲሁም የጠላት ሀይል ሳይበግራቸው አንድ የአማራ ቤት ሰርተው ለተመለሱት የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች የቃል ኪዳን ምልክት የሆነችውን የአባቶቻችን የቃል ኪዳን አርማ የሆነችውን ሰንደቅ ዓላማ በማበርከት ለቀጣይ መሪነት ዝግጁ እንዲሆኑ ተደርጓል:: በመጨረሻም የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ም/ል መሪ በአርበኛ ኢሳያስ ደመቀ የአፄ ዘርአያዕቆብ ኮር አንድ መሪ ሁነው የተመደቡ የፋኖ አመራሮች ቃለመሀላ እንዲፈጽሙ ተደርጎ የተመደቡ አመራሮች የአማራ ህዝብ የጣለባቸውን አደራ በብቃት እንዲወጡ ጭምር መልእክት በማስተላለፍ እና ከብልጽግና ጋር ወግነው ለሚሰሩ አመራሮች፥ የአድማ ብተና ፥የሚኒሻ ፥ እና የመከላከያ አባላት የፋኖን ትግል እንዲደግፉ ጥሪ በማስተላለፍ ፕሮግራሙ ተጠናቋል:: የኮሩን አመራሮች ዝርዝር ሙሉ መረጃ እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።             "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን" አፋብኃ ደቡብ  አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ዜና ክፍል        ጳጉሜ 03/2017 ዓ.ም
AM
0
1
9
743
News
News@NISIRInternati1·
አማኑኤል ከተማ ላይ ኦፐሬሽን ተሠርቷል። በአፋብኃ ምዕራብም አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር በላይ ዘለቀ ብርጌድ ጳጉሜን 02 ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ አማኑኤል ከተማ ላይ በሰራው ኦፐሬሽን ወርቄ አታላይ የሚበል የስርአቱ ተላላኪ ባንደ እስከመጨረሻው የሸኘ ሲሆን  አራት የወራሪውን ኃይሎች ቆስለኛ ማድረግ ችሏል። ጳጉሜን 03/13/2017 ዓ.ም
AM
0
0
1
317
News
News@NISIRInternati1·
ሰበር_ዜና አማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የልጅ እያሱ ኮር ክፍለጦሮች በጋራ በከፈቱት ጠንካራ ውጊያ የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ የሆነችውን #ውጫሌ ከተማን ተቆጣጥረው ታላቅ ድል ተጎናፀፉ:: ዛሬ ጳጉሜ 03/2017 ዓ.ም አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ በልጅ እያሱ ኮር ስር ያሉ ክፍለ ጦሮች የደቡብ ወሎ ዞን የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ውጫሌ ከተማ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ በቀጠለው ተጋድሎ እስከ መሀል ከተማ በመግባት የየጁ ክፍለ ጦር ራስ አሊ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ እና ራምቦ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ በጋራ በመሆን በተናበበ ፍፁም በተቀናጀ መልኩ የተሳካ ውጊያ በማድረግ ጠላትን ሙት እና ቁስለኛ ሲያደርጉት ውለዋል ። እስካሁን ከ10 በላይ ፖሊስ እና ሚሊሻ ሲገደል በቁጥር ያልተረጋገጠ የወራሪው መንግስት ወታደር ሚሊሻ አድማ ብተና አና ፖሊስ ቁስለኛ ሆኗል:: በተጨማሪም ሶስት የሚሊሻ አባላት ምርኮኛ በማድረግ ውጊያው እንደ ተፋፋመ ቀጥሏል:: በዚህ ውጊያ የልጅ እያሱ ኮር የበቀል በትሩን አጠናክሮ በመቀጠል ውጫሌ ከተማ ያለውን የብልፅግና ግብስብሰ የፀጥታ ኀይል እና ካድሬ እያጠራ ይገኛል፡፡ የአብይ ሠራዊት ከወልድያ እና ከደሴ ሁለት ዙ23 እና አንድ መድፍ ያመጣ ቢሆንም ከብዙ ኪ.ሜ ርቀት ቆሞ ከመተኮስ በዘለለ ምንም ፋይዳ ያለው ተግባር ሊፈፅሙ አልቻሉም፡፡ በተጨማሪም በተደረገው ከፍተኛ የከበባ ውጊያ አንድ ከፍተኛ (ኮሎኔል ሊሆን እንደሚችል ይገመታል) የመከላከያ አመራርም ጭምር ተገድሏል። ጠላትን ከበባ ውስጥ በማስገባት ውጊያው አሁንም የቀጠለ ሲሆን ከዚህ የተሻለ ጮቤ የሚያስረግጥ ድል እየጠበቅን ከበባውን አጠናክረን ይዘናል፡፡ መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ©አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የልጅ እያሱ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል 03/13/2017 ዓ.ም
AM
0
0
1
350
News
News@NISIRInternati1·
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን ህዝባዊ ውይይቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል(አፋብኃ)  ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ከሚያስተዳድራቸው ወረዳዎች አንዱ በዋግኸምራ አስተዳደር ዞን ጋዝጊብላ ወረዳ ላልኪው ቀበሌ አንዱ ሲሆን ከቀበሌው ማህበረሰብ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጉ ተነገረ። ጷግሜ 02/2017ዓ.ም የኮሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በተደረገው ህዝባዊ ውይይት የፋኖ ሰራዊት ከማህብተሰቡ ጋር ያለው ግንኙነት፣የሲቪል አስተዳደሩ ከህብረተሰቡ  እና ከሰራዊቱ ጋር ያለው ግንኙነት እንዲሁም የፍትህ አሰጣጥን በተመለከተ ሃሳቦች የተነሱ ሲሆን በተነሱ የመወያያ ሀሳቦች ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስና የቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መጠናቀቁ ታውቋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ  ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ        ጷግሜ 03 / 2017 ዓ.ም
News tweet media
AM
0
1
8
658
News
News@NISIRInternati1·
151 የአገዛዙ ወታደር እጅ ሰጠ በጎንደር ቀጠና 151 ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጃቸውን ለፋኖ ሲሰጡ፡ አገዛዙ ደግሞ የከዱትንና የሞቱበትን ለመተካት መጠነሰፊ የግዳጅ አፈሳ እያካሄደ ይገኛል። እስካሁን ባለው ሁነት ከጎንደር ከተማና አካባቢዋ በርካታ ወጣቶች በአገዛዙ ሀይሎች በግዳጅ ታፍሰዋል። ጳግሜ 2/2017/
AM
0
0
0
342
News
News@NISIRInternati1·
ሰበር የድል ዜና ዛሬ ጳጉሜ 02/2017 ዓ.ም አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ በልጅ እያሱ ኮር ስር ያሉ ክፍለ ጦሮች  የደቡብ ወሎ ዞን የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ውጫሌ ከተማ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ በቀጠለው ተጋድሎ እስከ መሀል ከተማ በመግባት የየጁ ክፍለ ጦር ራስ አሊ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ እና ራምቦ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ በጋራ በመሆን በተናበበ ፍፁም በተቀናጀ መልኩ የተሳካ ውጊያ በማድረግ ጠላትን ሙት እና ቁስለኛ ሲያደርጉት ውለዋል ። እስካሁን ከ 10  በላይ ፖሊስ እና ሚሊሻ ሲገደል በቁጥር ያልተረጋገጠ የወራሪው መንግስት ወታደር ሚሊሻ አድማ ብተና አና ፖሊስ  ቁስለኛ ሆኗል በተጨማሪም ሶስት የሚሊሻ አባላት ምርኮኛ በማድረግ ውጊያው እንደ ተፋፋመ ቀጥሏል:: በዚህ ውጊያ የልጅ እያሱ ኮር የበቀል በትሩን አጠናክሮ በመቀጠል ውጫሌ ከተማ ያለውን የብልፅግና ግብስብሰ የፀጥታ ኀይል እና ካድሬ እያጠራ ይገኛል፡፡ የአብይ ሠራዊት ከወልድያ እና ከ ከደሴ ሁለት ዙ23 እና አንድ መድፍ ያመጣ ቢሆንም ከብዙ ኪ.ሜ ርቀት ቆሞ ከመተኮስ በዘለለ ምንም ፋይዳ ያለው ተግባር ሊፈፅሙ አልቻሉም፡፡በተጨማሪም በተደረገው ከፍተኛ የከበባ ውጊያ አንድ ከፍተኛ የመከላከያ አመራርም ጭምር ተገድሏል።የከበባ ውጊያው አሁንም  የቀጠለ ሲሆን ከዚህ የተሻለ ጮቤ የሚያስረግጥ ድል እየጠበቅን ከበባውን አጠናክረን ይዘናል፡፡ አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ የልጅ እያሱ ኮር ህዝብ ግንኙነት ጳግሜ 2/2017/
News tweet media
AM
2
8
25
1.6K
News
News@NISIRInternati1·
የተከበራችሁ በውጭው ዓለም የምትኖሩ የኅልውና ትግላችን ደጋፊ ወገኖቻችን፣ የተከበራችሁ በሞት፣ በመፈናቀል፣ በሰቆቃ ላይ የምትገኙ ግፉአን አማራዎች፣ የተከበራችሁ የአማራውን ሥርዓታዊ ግፍ በሃሳብም በግብርም የምትቃወሙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፣ ክቡራትና ክቡራን!!! ከሁሉ አስቀድሜ ከሠላማዊ ትግል እስከ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግላችን ውድ ሕይወታቸውን ለከፈሉ የትግሉ ሰማዕታት ያለኝን ታላቅ አክብሮት መግለጽ እፈልጋለሁ። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በጽኑ አለት ላይ የተመሠረተ የአማራ ሕዝብን በአራቱም አቅጣጫ አቅፎ የሚያታግል ተቋም መሆኑን እየገለጽኩ ተቋማችን አፋብኃ መሠረቱ የትግሉ ሰማዕታት ደምና አጥንት ባይሆን ኖሮ ከውስጥም ከውጭም በተሰማሩ የጠላት አንጃዎች ፈርሰን፣ ተበትነን ነበር። ቅሉ የያዝነው ትግል መሠረቱ የትግሉ ሰማዕታት የተሰውለትን እውነት፣ የታገሉበትን ዕውቀት፣ የመከሩበትን ሐቀኛ አመክንዮ ያነገበ በመሆኑ ወደፊት ከመወንጨፍ ውጭ አማራጭ ስለሌለው በጽናት ከዛሬ ደርሰናል። የአፋብኃ ሠራዊት የጽናት ምንጩ አንዲት የማትተካ ሕይወታቸውን ለሕዝባቸው፣ ለታሪካቸው፣ ለባሕላቸው፣ ለእምነታቸው በጥቅሉ ለአማራዊ ማንነታቸው አሳልፈው የሰጡት የእነ ሜጀር ጄኔራል ውባንተ አባተ፣ የእነ አርበኛ ዮሐንስ ዓለማየሁ፣ የእነ አርበኛ ሳጅን አደም አሊ (አባ ናደው)፣ የእነ አርበኛ ሃምሳ አለቃ አባይ እንዲሁም የግፍ ግዞተኛው የአርበኛ አሰግድ መኮንንም የአደራ ቃል ነው። ስለሆነም መራብን፣ መቁሰልን፣ ብርድና ሙቀቱን ሁሉ ሕይወትን ከመስጠት በታች ነውና በጽናት ታግሰን፣ ሐቀኛ የመርኅ ተቋም እንድንፈጥር በሕይወት የተለዩን አርበኞች ምኞት ነበራቸውና ለምኞታቸው ማሳኪያ፣ ለዓላማቸው ማስፈጸሚያ እንዲሆን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይልን (አፋብኃ)ን መሠርተን በመታገል ላይ እንገኛለን። ክቡራትና ክቡራን ወገኖቻችን፦ • አፋብኃ የተሰው የትግሉ ሰማዕታት በደማቸው ቀለምነት ከትበው የሰጡን የአደራ ቤታችን ነው። አፋብኃ በየማጎሪያ ቤቱ በአማራዊ ማንነታቸው በግዞት የሚማቅቁ ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች ነጻ መውጫ ተቋም ነው። አፋብኃ በዘር ተኮር ጭፍጨፋ መዋቅራዊ አዋጅ የተጨፈጨፉ ሕጻናት፣ ሴቶች፣ አረጋውያን የሰቆቃ ድምጽ እረፍት የሚነሳው የትግል ተቋም ነው። o አፋብኃ ውስጥ ሕጻን አይሻ መሃመድ አለች፣ o አፋብኃ ውስጥ ሃምሳ አለቃ አባይ አለ፣ o አፋብኃ ውስጥ ሜ/ጄ ውባንተ አባተ አለ፣ o አፋብኃ ውስጥ ሳጅን አደም አሊ አለ፣ o አፋብኃ ውስጥ ዮሐንስ ዓለማየሁ አለ። በመሆኑም አፋብኃ በአርበኝነት የተሰው ጓዶቻችን አደራ፣ ምኞት እንዲሁም በሕይወት የሚገኙ አደራ ተቀባይ ታማኝ አርበኞች የነፍስ ትስስር፣ አማራዊ ተጋምዶ የተሸመኑበት ተቋም መሆኑን አውቃችሁ ለዓላማችን መሳካት የሕይወት ዘመን ባለቤቶች ጭምር እንድትሆኑ ነው ይህ ሲምፖዚዬም የተዘጋጀው። • አፋብኃ በእውነት፣ ለእውነት፣ ስለእውነት የጀመርነውን ትግል ቅርጽ ፈጥሮ፣ መርኅ ሕግ እና አሠራር አበጅቶ የተገባደደውን ትግላችንን መቋጫ ተቋማችን በመሆኑ በአንድ ጎን እንተኩሳለን፣ በአንድ ጎን እናሰለጥናለን እናደራጃለን፣ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲ፣ አድቮኬሲና ፕሮፓጋንዳ እንሠራለን። እነዚህን ሁሉ ሥራዎች ለማከናወን ብዙ የሙያ ስብጥር፣ በርካታ የሰው ኃይል አስፈላጊ ስለሆነ አፋብኃን ከመደገፍ አፋብኃ ወደ መሆን ትሸጋገሩም ዘንድ ጥብቅ ጥሪ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ። ክቡራትና ክቡራን ወገኖቻችን፦ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ድርጅታዊ መርኅን አክብሮ፣ የሕዝባችንን ኅልውና በዘላቂነት ለማረጋገጥ አስቻይ የአንድነት መደላድሎችን በሰከነ ውይይት ፈትቶ እንደሚታገል በተደጋጋሚ ገልጸናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በመላው ዓለም የምትገግኙ ወገኖቻችን • የሙያ ተደጋግፎት፣ • የዓላማ ተደጋግፎት፣ • የአማራዊነት ተደጋግፎት ፈጥራችሁ በምትኖሩባቸው ከተሞች ሁሉ አንድ እንድትሆኑ፣ ምን እናድርግ በሚል ሁለትም፣ ሦስትም፣ በርካታም ሆናችሁ በጋራ እንድትመክሩ፣ ስለአንድነት እንድትመክሩና በማኅበራዊ ሚዲያ፣ በፎክ ሚዲያ፣ በሜንስትሪም ሚዲያ የሚደረጉ መነቃቀፎችን፣ የሚቀርቡ ዘለፋዎችንና ፍረጃዎችን አስወግዳችሁ • አንድ ዓይነት ጩኸት፣ • አንድ ዓይነት ቋንቋ፣ • አንድ ዓይነት ትንፋሽ፣ • አንድ ዓይነት እርምጃዎችን ልንራመድ የምንችለው ስንቀራረብ፣ ስንነጋገር፣ አንድ ስንሆን ብቻ መሆኑን አውቃችሁ አንድ ሁኑ፣ አደራ አደራ አደራ አንድ ሁኑ። ያኔ በሁሉም ዘርፍ ተጽእኖ ፈጣሪዎች መሆን እንችላለን። • ዓለም የተጽእኖ ፈጣሪዎች፣ • ድል አድራጊነትም የተጽእኖ ፈጣሪዎች ስለሆነች ድል አድራጊነታችንን በአጭር ጊዜ እንድናደርገው አንድ እንሁን፣ ዓለም አቀፋዊ ተጽእኖም እንፍጠር። ያኔ በቀናት ውስጥ አይደለም በሰአታት ውስጥ እናሸንፋለን ማለት እፈልጋለሁ። ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) አርበኛ ኢንጂኒዬር ደሳለኝ ሲያስብሸዋ አመሠግናለሁ። ጳግሜ 2/2017/ዓ.ም
News tweet media
AM
0
11
31
1.9K
News
News@NISIRInternati1·
➾አርበኛ ዘመነ ካሴ በአፋብኃ ሲምፖዚየም ያስተላለፈው ታሪካዊ መልዕክት እና ድንቅ ንግግር‼ የተከበራችሁ የዚህ ውይይት ተሳታፊዎችና ተከታታዮች ክቡራን የማሕበራት ተወካዮች የተወደዳችሁ የመገናኛ ብዙሃን ሙያያተኞችና ድርጅቶች ውድ የድርጅታችን አፋብኃ አመራሮችና የሠራዊታችን አባላት ሁላችሁም በመላው ዓለም ያላችሁ አማራዎችና የአማራ ወዳጆች፤ በቅድሚያ የአክብሮት ሠላምታዬ ይድረሳችሁ!! ከትናንት ጀምሮ እየተካሔደ ያለው ውይይትና እየቀረበ ያለው መልዕክት የአማራ ወገናችን ራሱን ከፈፅሞ ጥፋት ለመታደግ የሚያደርገው የሕልውና እና የፍትሕ ርትዕ ትግል አንድ ሁነኛ መገለጫ ነው። ዛሬ በዚህ መድረክ ተሰባስበን ስንመክር በአማራነታችን ላይ የታወጀውን ጥፋት ለመመከት፡ ከምንግዜውም በላይ ንቃት ፈጥረን፡ አደረጃጀት አበጅተን፡ የትናንትን ጉድለት በዛሬ ጥረት አሟልተን ፡ነጋችንን የተሻለ የማድረግ ቁርጠኝነታችንን የምናድስበት ነው። ባለፉት ሁለት ዓመታት የአማራነት ንቃትና መሰባሰብ ከእነውስንነቶቹ  አመርቂ የሚባል እድገት አሳይቷል። ግዙፍ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም በመፍጠር የመደራጀት ያደረ የቤት ስራችንን መመለስና ማረም ጀምረናል!! በአማራነት ላይ የተፈጠረው ንቃትና መሰባሰብ የዘመናት የጥቃት አዙሪትን ለመስበር በሚያስችል ግለት ውስጥ ይገኛል። ባለፉት ሁለት ዓመታት ራሳችንን አጠናክረናል !! ለሕልውናው የሚሰለፍ ሕዝባዊ ኃይል ፈጥረናል!! ሊያጠፋን የተነሳውን ጠላት በመመከት ማሸነፍ እንደምንችል አረጋግጠናል !! የዕጣፈንታችን ወሳኞች እኛ ነን ብለን ስንነሳ የመናጆነት፣ የተከታይነት፣ የአጃቢነት ልማዶችን ሰብረን የአማራዊ ማንነታችን እና ፍላጎቶቻችን በአማራ ልጆች የሚወሰንበት ምዕራፍ ለመክፈት ነውና ጀምረነው ብዙ ርቀት ሔደናል። የተከበራችሁ የዚህ መድረክ ተሳታፊዎች፤ አማራዎች ራሳችንን ብሎም አገራችንን ለማዳን አብዛኛውን የትግል መንገድ ሞክረነዋል። በዜግነት ፖለቲካና በአገር አንድነት ትግል አልፈናል። ሆኖም በአማራነታችን ላይ የታወጀውን ጥፋት አልመከትነውም። በዚያ መንገድ ኢትዮጵያን ከመስቀለኛ መንገድ መታደግ አልተቻለም። አሁን ለረጅም ጊዜ ያልሔድንበት በአማራነት ተደራጅቶ ራስን የመታደግ ትግል የጊዜው ቁልፍ ተልዕኮ ነው። አማራና አማራነት የዚህ ዘመን ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡ በአማራነት ላይ በተከፈቱ ጥቃቶች ውስጥ ገና ከማለዳው እነደጃዝማች ፀሐዩ እንቁስላሴ የገለጡት የወል ጥቃት መረዳት ተዳፍኖ የቀረ ነበር። ኋላም እነፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያነሳሱት የአማራ ንቃት ቅስቀሳ ብዙም ሳይሻገር ቀርቷል። በረጅሙ ታሪካችን ውስጥ አማራነታችን ላይ ጥቃቶች በቀጠሉበት፥ በአማራነት መሰባሰብ እና የጋራ ተቋም መፍጠር ሳንችል ቀርተን አማራን የሚያሕል ሕዝብ የሕልውና አደጋ ውስጥ ይገኛል። ተቃርኖው ይገርማል !! አገር የመሠረተ ሕዝብ ፣ ይብዛም ይነስም የአገሪቱን ተቋማት የመሠረተና የመራ ሕዝብ፣ ለሺህ ዘመን ፀንተው የቆሙ መንፈሳዊ ተቋማትን ያደራጀ ሕዝብ ፣ ለዘመናት አገር የጠበቀ አርበኝነት ያለው ሕዝብ ፥ ራሱን ከሕልውና ጥቃት የሚመክትባቸው ተቋማት አጥቶ ዛሬ ላይ ደረሰ። አማራዎች ራሳችንን የምንጠብቅበት ሥርዓት፣ ፍላጎታችንን የምንገልጥባቸው አማራዊ ተቋማትን መፍጠር ዳገት ሆኖብን መኖራችን መገታት አለበት። ይህ ትግል "የአማራን ሕዝብ ሁለንተናዊ ሕልውና በዘላቂነት የማረጋገጥ ነው" ስንል የሕልውና መሠረቶቻችንን የሚሸከሙ ተቋማትን የመትከል መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም። የፋኖ አንድነት ተቋማዊ ጉዞ የዚያ ምሰሶ ይሆናል!! በአማራነት ተለይቶ መጠቃት በታወጀበት ዘመን እንኳ አባቶቻችንና እናቶቻችን ስለአገር እንጂ ስለአማራነታቸው አልመከሩም ፡ አልተሰባሰቡም፡  አልተደራጁም። ስለአገር ዋጋ መክፈላቸው ባልከፋ ፥ ሲከፍሉት የኖሩት ዋጋ ግን በአማራነታቸው ላይ የተከፈተውን የጥፋት ጦርነት ሊያስቆመው አልቻለም። የትናንት አለመደራጀት ለዛሬ ያወረሰን ምን እንደሆነ በውል ተገንዝበን ተነስተናል !! ትናንት ያልሠራነው ሥራ ቁጭት ካወረሰንና ለዛሬ ብርቱ ትግል ስንቅ ከሆነን በቂ ነው። ነጋችንን የምናሳምረው ግን በዛሬ የተባበረ ጥረታችን ነው!! ይሕ ትውልድ ለነገ የሚያሻግረው የጥቃት ውርስ ሊኖር አይገባም !! ይሕ የእኛ ትውልድ  የቤት ሥራውን ሳይሠራ ቀርቶ የነገው ትውልድ ጥፋትን እና ፈፅሞ መገፋትን ሊወርስ አይገባም!! ስለዚህ እንሰባሰብ !! በአማራነታችን እንደራጅ !! በአማራነት የመደራጀትና የመታገል ጉዳይ ግለሰባዊ እና ጠባብ ቡድናዊ ፍላጎትን መተው ይፈልጋል። በመካከለችን ያለ ትናንሽና መለስተኛ ቅራኔና ፀብን፥ ኩርፊያና ልዩነትን በመተውና በማቆየት ለወል ፍላጎታችን መሰለፍን ይጠይቃል። ብሔርተኝነት እንደዚያ ነው !! ከትናንትም ሆነ ከዛሬ ነገሮቻችን መካከል መርጦ መዘንጋት እና ለይቶ ማንሳትን ይፈልጋል !! ስለጋራ አማራዊ ፍላጎታችን የመሰለፍ ጥሪ ነው !! ያን ስናደርግ እንኳን ለአማራ ትውልድ፥ ለኢትዮጵያ እና ለሰው ልጆች ሁሉ የሚተርፍ ቁምነገር እንሠራለን!! የጋራ ጥቃት አንገሽግሾን የወጣን ታጋዮች ሁሉ እንደአማራ ስንመክር፣ እንደፋኖ ስንነጋገር  ከባድ የመሠለን ቀላል እንደሚሆን አይተናል። የራሳችንን ጉዳዮች በራሳችን ለመወሰን "የእብድ ገላጋይ..." አያሻንም።   እናም የጀመርነው የአንድነት ጉዞ የተማከለ አማራዊ አታጋይ ተቋም በመመስረት የሚቋጭ ይሆናል። ይሕ የአዲሱ አመት ድላችን ሆኖ ይመዘገባል!! የተወደዳችሁ የሕልውና ትግሉ ተሰላፊ ምሑራንና ማሕበራት፤ ያለነው እንቅልፍ አልባ ዘመን ነው። እኛን ለማጥፋት ፍፁም ጭካኔ እና ሙሉ ቆራጥነት ያለው ገዢ ጠላት ነው የገጠመን። የምናሸንፈው ከአጥፊው ጠላታችን በላይ ስንጨክን፣ ከገጠመን ደመኛ በላይ ስንተጋ፣ ከእነሱ በላይ ስንደራጅና አንድ ስንሆን፣ ከጠላቶቻችን በላይ ቆራጦች ስንሆን ነው። ከእነሱ በላይ ስንሠራ እንጂ በእነሱ ልክ እየተራመድንም አይደለም። ስለሆነም በዓለም ዙሪያ ያላችሁ የአማራ ምሑራን፣ የዲያስፖራ ማሕበራት፣ ሰፊው በወጭ አገር ያለህ ወገናችን እንድትሰባሰቡ በአንድ እንድትቆሙ ጥሪ ማቅረብ እፈልጋለሁ። ስለወገናችን የምንቻቻልበት፣ ስለራሳችን የምንመክርበት፣ የምንተሳሰብበት ፣ በእያንዳንዳችን ላይ ልዩ ተልዕኮ የወደቀብን ወቅት አሁን ነው። ከዚህ ወቅት በቀር ስለአማራና አማራነት የምንሰለፍበት የምንሠራበት የተለየ ጊዜ የለም። ዛሬ ነው !! እናም የአማራ ማሕበራት ከተበታተነ ጉዞ ውጡና ተሰባሰቡ!! በየአሕጉሩ አንድ ጠንካራ ሕብረት አቁሙ!! ምሳሌ ሁኑ!!  የአንድነት ፤ የዲፕሎማሲ ፣ የአድቮኬሲና ትብብር ምሳሌ ሁኑ!! በመጨረሻ ግን በዋነኛነት ፥ በመላው ዓለም የምትገኙ ማሕበራት፣ ምሑራንና መገናኛ ብዙሃን ሁሉንአቀፍ አማራዊ ጉዳዮቻችን የሚመከሩበት "የአማራ የምክክር ጉባኤ" በፍጥነት እንዲዘጋጅ ጥሪ አቀርባለሁ። አርበኛ ዘመነ ካሴ የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድና አባልና የምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ ሰብሳቢ አዲስ ትውልድ፣ አዲስ ተሰፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ ጳግሜ 2/2017/
AM
0
3
8
639
News
News@NISIRInternati1·
ሰበር መረጃ!! ምስራቅ ወለጋ ዞን ኪረሙ ወረዳ ሀሮ አዲስ አለም ከተማ ፋኖ ቤተሰብ አላቹህ የተባሉ ንፁሀን አማራዎች በሙሉ ከቤታቸው እንዲወጡ እዬተደረገ ቤታቸው እዬታሸገባቸው ይገኛል። እንደምንጮች ገለፃ አማራ ላይ የተከፈተው የተቀናጀ ጥቃት በሁሉም ወለጋ ዞኖች ተባብሶ ቀጥሏል።በወለጋ አሁን የተያዘው አማራን ከወለጋ ማፅዳት የሚል ፕሮጀክት ነው ሲሉም ነው ምንጮች የገለፁ። ጳግሜ 2/2017/
AM
1
0
1
298
News
News@NISIRInternati1·
የአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ የሐዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክ/ጦር የየቦቅላ አባይ ብርጌድ በቀን 02/13/2017 ዓ.ም ደብረ ማርቆስ ላይ ልዩ ኦፕሬሽን ሰርቷል። ከተማ በመግባት አብማ ቀበሌ 04 ሙሉ ሆቴል ጀርባ ጎጆ መሿለኪያ አካባቢ የአረመኔው አገዛዝ ሰራዊት መመሸጊያ ላይ መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም በቦታው የነበሩ ምሊሻዎችን ሙትና ቁስለኛ አድርገዋል።በባንዳ ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ከጉንደ ወይን ወደ ደብረ -ወርቅ ኮፖይ አድርሶ ሲመለስ ከቀኑ 8:30 ሠዓት ሽፋሬ በምትባል ንዑስ ከተማ ላይ 9ኛ ሳሙኤል አወቀ ክ/ጦር የሶማ ብርጌድ ጥቂት ሀይሎች ደፈጣ በመያዝ  አድማ ብተና በጫነ ካሶኒ ላይ የቦንብና የጥይት በረዶ በማዝነብ  ከፋተኛ ጀብ መፈፀም ተችሏል። በጠላት ላይ የደረሰ ኪሳራ፦6 የአድማ ብተና አባላት በቦንብ ተጨፍልቀው እሰከወዳኘው ሲሸኙ አራት የሚሆኑት የአድማ ብተና አባላት ደግሞ ከባድ ቁስለኛ ሁነው በፈለገ-ብርሀን ጤና ጣቢያ ውስጥ ይገኛሉ።የበተመሳሳይ አባኮስትር ብርጌድ የደፈጣ ጥቃት ሲፈፅም አብራጅት ብርጌድ ደግሞ የላምጌጅ ከተማን ተቆጣጥሮ ውሏል።ይህ በየቦታው በሚደረገው ጥቃት የደከመው አረመኔ ሰራዊት በገፍ እጁን ለፋኖ እየሰጠ ይገኛል። 1ኛ. አዲሱ ሞላ ከአድማ ብተና ተቀም ወደ አፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ 1ኛክ/ጦር ባህርዳር ብርጌድ ጊወንሻለቃ የተቀላቀለ ። 2ኛ.ናትናኤል አበበ የሬጅመንት ሶስት ሞርተር ምድብተኛ ከጠላት ካንፕ በመክዳት ወደ አፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ ጎጃም አገዉ ምድር ፫ኛ ክ/ጦር፣ የቢትወደድ አያሌዉ መኮነንን ብርጌድን የተቀላቀለ። 3ኛ.ሀብታም መለሰ የሚባል የአረመኔው አገዛዝ አሽከር የነበረ ሚሊሻ የአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ የሐዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክ/ጦር አብራጂት ብርጌድን ተቀላቅሏል። 4ኛ.አበረ ገበረጌታ የተባለ የአረመኔው አሽከር ሚሊሻ ከየጁቤ ከተማ በመውጣት የአብራጂት ብርጌድን የተላቅሏል። 5ኛ. እውነቱ ምትኩ የተባ  የሚኒሻ አባል ከደብረ -ወርቅ ከተማ በመክዳት  9ኛ ሳሙኤል አወቀ ክ/ጦር ሶማ ብርጌድ ተቀላቅሏል። ሕዝባዊ ውይይቶችና ምክክሮች በአንደኛ ክፍለጦር እና 7ኛ ክፍለጦር  ነፃ ቀጠና ቀበሌዎች ተደርገዋል። በውይይቱም ሌቦችን በጥቆማ መያዝ እና የማያዳግም እርምጃ መውሰድ ተችሏል። አፋብኃ|ቴዎድሮስ ዕዝ ጳጒሜን 02/2017ዓ.ም
AM
0
0
0
257
News
News@NISIRInternati1·
ሦስት የፖሊስ አመረራሮች ተገደሉ የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ በሚል የሦስትና የአራት ዓመት ህፃናትን ጨምሮ በርካታ እናቶችንና አረጋውያንን ለእስር በመዳረግ ግፍና መከራ ሲፈፅሙ ነበር የተባሉ ሦስት የፖሊስ አመራሮች ከነ አጃቢዎቻቸው ተገደሉ።የፖሊስ አመራሮቹ የተገደሉት በተፈፀመባቸው የደፈጣ ጥቃት ሲሆን፡ ተሳፍረው ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱበት የነበረው ወታደራዊ ፓትሮልም ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተሰምቷል። ሕሊናቸውን በሆድ ቀይረው፡ አገዛዙ በወገናቸው ላይ ለሚፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ ተባባሪ በሆኑ የፖሊስና የሚሊሻ እንዲሁም የአድማ ብተና አባላት ላይ የሚወሰደው ጥብቅና ከባድ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ፋኖ አስታውቋል።በደቡብ አማራ ቀጠና ኤፍራታና ግድም ወረዳ በቆሪ ሜዳ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቀርሣ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ላይ ትናንት ጳጉሜ 01/2017 ዓ/ም አመሻሹን በተፈፀመ ደፈጣ ጥቃት ሦስት የፖሊስ አመራሮችና አምስት የአመራሮቹ አጃቢዎች መገደላቸውን የአሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ካወጣው መረጃ ለማወቅ ተችሏል። የፖሊስ አመራሮቹ፡ "ፋኖ ናችሁ፣ የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ፣ የፋኖ ደጋፊ ናችሁ" በሚል የሦስትና አራት ዓመት ህፃናትን ጨምሮ በርካታ የወረዳው ነዋሪዎችን ለእስር በመዳረግ ሲያሰቃዩና አንዳንዶቹንም ከእስር እንዲለቀቁ ከ50ሺ ብር ጀምሮ እስከ አንድ መቶ ሺ ብር ድረስ እንዲከፍሉ በመጠየቅ ግፍና መከራ ሲፈፅሙ የነበሩ ናቸው ተብሏል። በእነዚህ የፖሊስ አመራሮች ትዕዛዝ ሰጭነት ታስረው የጠተየቀባቸውን ገንዘብ መክፈል ካልቻሉ ንፁኋኖት መካከል፡ "ለፋኖ ሲሰልሉ የተገኙ" ተብለው እንዲረሸኑና አንዳንዶቹም ከድብደባ ብዛት ከባድ የአካል ጉዳት እንዲደርስባቸው የተደረጉ ስለመኖራቸውም ተነግሯል።በእነዚህ ፀረ ሕዝብና የነፃነት አሜካላ እሾዎች ላይ የተጠናና ስኬታማ የሆነ ደፈጣ ጥቃትን በማካሄድ ግድያውን የፈፀሙት በአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና ብርጋዲየር ጄነራል አሳምነው ፅጌ ዕዝ ዓፄ ይኩኖአምላክ ክ/ጦር ስር የሚገኙት "ፀያይሞቹ አናብስት" የሚል ቅፅል ስም ያላቸው የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ብርጌድ የቃኝ አባላት መሆናቸውን ነው ከዕዙ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ለማረጋገጥ የተቻለው። ትናንት ጳጉሜ 01/2017 ዓ/ም አመሻሹን ደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመው በኤፍራታና ግድም ወረዳ ቆሪ ሜዳ ቀበሌ ልዩ ስሙ ቀርሣ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ሲሆን፡ በዚህም ፋኖ የሕዝቡን እምባ  ያበሰ እጅግ ትልቅ ድል መቀዳጀቱ ነው የተነገረው።አመራሮቹ ደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመባቸው በልዩ ዞኑ ስር በምትገኘው ከጨፋ ሮቢት ከተማ ወደ አጣየ ከተማ እየተጓዙ ባሉበት ሁኔታ ነው የተባለ ሲሆን፡ ደቂቃዎችን ባልፈጀ ኦፕሬሽን በግፈኞች ላይ የመጨረሻውና ከባዱ እርምጃ ተወስዶቸዋል ተብሏል።በዚህ ደፈጣ ጥቃት ሦስቱ የፖሊስ አመራሮችን ጨምሮ አምስት አጃቢዎች በድምሩ ስምንት ፀረ ሰላምና ፀረ ሕዝብ ኃይሎች መገደላቸው ታውቋል።በጥቃቱ ከተገደሉት አመራሮችና የአመራሮቹ አጃቢዎች በተጨማሪ፡ ተሳፍረው ከቦታ ቦታ ሲንቀሳቀሱበት የነበረው ወታደራዊ ፓትሮልም ሙሉ በሙሉ መውደሙን ዕዙ አስታውቋል። ሕሊናቸውን በሆድ ቀይረው፡ አገዛዙ በወገናቸው ላይ በሚፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ እንዲሁም ግፍና በደል ተባባሪ በሆኑ የፖሊስና የሚሊሻ እንዲሁም የአድማ ብተና አባላት ላይ የሚወሰደው ጥብቅና ከባድ እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ፋኖ አስታውቋል።
News tweet media
AM
3
7
28
2.3K
News
News@NISIRInternati1·
ደ/ኤልያስና አካባቢው ላይ የመሸገው የብልፅግና ስርዓት ሀይል ንፁሀንን እየዘረፈና ንብረቶቹን እያወደመበት ይገኛል። በቀጠናው የዘረፋና የውንብድና ስራዎች በአገዛዙ ዘራፊና አሸባሪ ቡድን ተጠናክሮ ቀጥሏል።የቀጋት ቀበሌ ልዮ ቦታ ጋርማ በምትባል ቦታ አቶ አንማው ተመስገን ከተባሉ ሽማግሌ ቤት በቀን 27ለ28/12/2017 ዓ.ም ሌሊት ፊታቸውን ጭንብል በመልበስ በወረዳዋ የተሰባሰቡ ሰላም አስከባሪ ነን የሚሉ የመንግስት ዘራፊና አሸባሪ ቡድኖች 1ኩንታል ስንዴ አንድ ኩንታል ዱቄት አንድ የአንገት ክታብ ከነሁለት ብር ቅጥል 1ድፍን ብር ቅጥል (ውድ ጌጣጌጦችን) በመዝረፍ ተሰውረዋል። ለዘረፋና ለውንብድና የተሰማሩት የአሸባርሪው አገዛዝ ቡድኖች ይህን እኩይ ድርጊት የፈጸሙት ፋኖ ነን በሚል ስም ሲሆን ፋኖን ከማህበረሰቡ ለመነጠል በማሰብ ነውና ማህበረሰባችን ይህን ሴራ መረዳት እና ፋኖ ይህን እኩይ ድርጊት እንደማያደርግ ማወቅ ይገባል። ሌላው የአማራውን ማህበረሰብ በኢኮኖሚ ለማዳከም በቀረጹት አጀንዳ መሰረት የማህበረሰብ ንብረቶችን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ እያቃጠሉ ይገኛል ሲል ቀስተ ደመና ብርጌድ አስታውቋል። ጷጉሜን 2/2017 ዓ.ም
News tweet media
AM
0
4
2
382