Sabitlenmiş Tweet
Daniel Daba
39.3K posts


የኬንያ እና የኡጋንዳ ፕሬዝዳንቶች የባህር በር ለሌላት ኡጋንዳ ወደ ህንድ ውቅያኖስ መውጫ የሚያስገኝላትን የባቡር መስመር ማስፋፊያ ፕሮጀክት በጋራ አስጀመሩ። ይህ የባቡር መስመር በዋነኝነት በኬንያው የሞምባሳ ወደብ ላይ ጥገኛ ለሆነችው ኡጋንዳ የጭነት ትራንስፖርትን በእጅጉ እንደሚያቀልላት ተገልጿል። በቻይና የተገነባው የስታንዳርድ ጌጅ የባቡር መስመር ማስፋፊያ ከኬንያዋ ኪሱሙ ከተማ ተነስቶ ከኡጋንዳ ጋር በሚያዋስነው የማላባ ድንበር ላይ ያበቃል።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ባደረጉት ንግግር፣ ይህ ከኪሱሙ እስከ ማላባ የተዘረጋው የባቡር መስመር መቼም ቢሆን መዳረሻ የሌለው ሆኖ እንደማያውቅ እና ይልቁንም የኬንያን ብልጽግና እንዲሁም መዋቅራዊ ለውጥ ለማረጋገጥ የታቀደ መሆኑን አብራርተዋል። በሌላ በኩል የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ በበኩላቸው፣ ይህ ፕሮጀክት ምክንያታዊ ያልሆነውንና አላስፈላጊ ወጪ የሚያስወጣውን የኡጋንዳን የትራንስፖርት ሥርዓት ለማስተካከል ትልቅ ሚና እንዳለው በመግለጽ፣ በቀጣይ ሁሉንም ከባድ ጭነቶች ወደ ባቡር መስመሩ ለማዛወር ማቀዳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ የባቡር መስመር ማስፋፊያ ቻይና የገንዘብ ድጋፏን ማቋረጧን ተከትሎ ከስድስት ዓመታት በላይ ተስተጓጉሎ የቆየ ነበር። የሞምባሳን ወደብ ከዋና ከተማዋ ናይሮቢ ጋር የሚያገናኘው የመጀመሪያው ምዕራፍ በ2017 የተጠናቀቀ ቢሆንም፣ ቻይና በ"ቤልት ኤንድ ሮድ" ማዕቀፍ ለአፍሪካ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች የምትሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ በመቀነሷ፣ ፕሮጀክቱ ከኡጋንዳ ድንበር ከ350 ኪሎ ሜትር በላይ ርቆ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ እንዲቆም ሆኖ ነበር። ይህ መስተጓጎልም የቀጣናውን ትስስር እና ንግድ ለማሳደግ ታቅዶ የነበረውን ድንበር ዘለል ግንኙነት ወደ ኋላ ጎትቶት ቆይቷል።
ፕሬዝዳንት ሩቶ አክለውም ፕሮጀክቱ የትራንስፖርት ወጪን ከመቀነሱም ባሻገር የአሰራር ቅልጥፍናን በማሻሻል ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ የባቡር መስመሩ ከ15 ሚሊዮን በላይ መንገደኞችን እና ከ45 ሚሊዮን ቶን በላይ ጭነትን አጓጉዟል። ከ2014 ጀምሮ ባለው ሂደትም ከጭነት አገልግሎት በየወሩ ከ1.3 ቢሊዮን የኬንያ ሺሊንግ በላይ ገቢ እያስገኘ ሲሆን፣ የመንገደኞች ገቢ ደግሞ በ40 በመቶ ማደጉ ተመላክቷል። ኬንያ አሁን ላይ ለአዲሱ ምዕራፍ ግንባታ መነሻ የሚሆን በዓመት 270 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የባቡር ልማት ቀረጥ ነባሩን መስመር ከሚጠቀሙ ጭነቶች ላይ እየሰበሰበች ትገኛለች። ቻይናም በቻይና መንገድ እና ድልድይ ኮርፖሬሽን በኩል በዋና ተቋራጭነት በማስፋፊያ ፕሮጀክቱ ላይ ተሳትፎዋን ቀጥላለች።

AM

Abraha Desta በትግርኛ እንደጻፈው
በአንድ በኩል “የፌዴራሉን መንግሥት ለመምታት ከሻዕቢያ ጋር ጽምዶ ፈጥረናል” እያልክ፤ ነጋዴዎችን በጉልበት እየሰበሰብክ ለጦርነት ገንዘብ እንዲያዋጡ እያስገደድክ፤ በሌላ በኩል “በጀት ስደድልን” ማለት “እንድመታህ በትርህን ስጠኝ” እንደማለት ነው።
የፌዴሬሽኑ አካል ሆነህ ሳለ በፌዴራሉ መንግሥት ላይ ጦርነት ማወጅና ያለ ፈቃድ ከ “ሌላ ጠላት መንግሥት” ጋር መገናኘት ህገወጥ ተግባር ነው።
የህወሓት ቡድን የትግራይ ህዝብን ወደ አደጋ ለማስገባት ህጋዊ ያልሆኑ ነገሮች እየሰራ ነው።
የክልል በጀት የሚጠየቀው በህጋዊ መንገድ ነው።
የክልል በጀት ለልማት እንጂ ለጦርነት እንዲውል አይፈቀድም። የፌዴራሉ መንግሥት ያልፈጸማቸው ነገሮች አሉ፤ እንዲፈጽማቸው ደግሞ በህጋዊ አሰራር መጠየቅ ይገባል።
ህጋዊ አካሄድ ትርጉም የሌለው ከሆነ (ኢትዮጵያ ውስጥ የህግ የበላይነት ስለሌለ) በፖለቲካዊ ድርድር መሞከር ያስፈልጋል።
ይህ ካልተቻለ ፖለቲካዊ ጫና መፍጠር ይቻላል።
መሬቴ ወይም ሌላ ንብረቴ አልተመለሰልኝም በሚል ወደ ጦርነት መግባት እምትችለው (እሱም እንደ መጨረሻ አማራጭ ነው) ሀገር ከሆንክ ነው።
ሀገር ከሆንክ ደግሞ ከጎረቤት ሀገር በጀት እንዲሰጥህ አይጠየቅም።
በየትኛውም መመዘኛ ጦርነት ማወጅና በጀት መጠየቅ አብረው አይሄዱም።
አስቡት እስቲ ህወሓት በፌዴራል ስልጣን ላይ እያለች የትኛውም ክልል (አማራ፣ ኦሮሚያ ወይም ሱማሌ) ህወሓት እያደረገው እንዳለው ብአዴን ወይም ኦህዴድ እምብኝ ቢል? ምን ያህል ቅጣት እንደሚወርድበት!?


AM

የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ከታሪካዊ ገናናነት እስከ ዳግም መነሣት…………
የኢትዮጵያ ሮያል ባሕር ኃይል በ1948 ዓ.ም በምጽዋ ወደብ መመሥረቱን ተከትሎ፣ በቀይ ባሕር ላይ የሀገራችንን ሉዓላዊነትና ብሔራዊ ጥቅም ሲያስከብር የቆየ ገናና ተቋም ነበር።
በደርግ ዘመነ መንግሥትም በትጥቅና በሰው ኃይል በላቀ ሁኔታ ቢደራጅም፣ በ1983 ዓ.ም የመንግሥት ለውጥን ተከትሎ ተቋሙ እንዲፈርስ መደረጉ ኢትዮጵያ ወደብ አልባ እንድትሆንና የባሕር በሯን እንድታጣ ምክንያት የሆነ "ጥቁር የታሪክ ጠባሳ" ሆኖ አልፏል።
የቀድሞው የባሕር ኃይል አባል ሌተናንት ሀለፎም መለሰ እንደሚሉት፣ በወቅቱ በተሸረበ ሴራ ኢትዮጵያ ይህንን ታላቅ ጥቅሟን እንድታጣ ተደርጓል።
ይሁን እንጂ ከ2011 ዓ.ም ወዲህ ተቋሙን ዳግም የመመሥረት ታሪካዊ ሥራ ተጀምሮ ወደ ተግባር ተገብቷል። የባሕር ኃይል አዛዥ ቫይስ አድሚራል ክንዱ ገዙ እንደገለጹት፤ የባሕር ኃይል መኖር በቀጣናው ካለው ውስብስብ ፖለቲካ፣ ከባሕር ላይ ወንበዴነት ስጋትና ከንግድ መርከቦች ደኅንነት አንጻር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
በቅርቡ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት የባሕር ላይ ወታደራዊ ልምምድ ላይ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ተሳታፊ መሆኑ፣ የተቋሙን ሕጋዊነትና የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ፍትሐዊነት ለዓለም ያሳየ ትልቅ ክስተት መሆኑንም ጠቁመዋል።
የባሕር ኃይል መገናኛ ሲስተም ኃላፊ ካፒቴን አበበ ዓለሙ እንደሚሉት፤ ከሩሲያ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ ጋር የተደረገው ልምምድ የተቋሙን የቴክኖሎጂና የክህሎት አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል በሰው ኃይልና በሥልጠና ራሱን በከፍተኛ ሁኔታ እያበቃ የሚገኝ ሲሆን፣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስከበርና ከባሕር የሚቃጡ ጥቃቶችን ለመመከት በትጋት እየሠራ እንደሚገኝ ከመከላከያ ሠራዊት ማሕበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል


AM

ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ጉዳይ ተመልካች ብቻ ሆና መቆየት አትችልም
********************
በአሁኑ ወቅት ዓለም ከአንድ ዋልታ ወደ ብዝኃ-ዋልታ የኃይል ሽግግር ውስጥ ትገኛለች። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ ደግሞ የቀይ ባሕር ቀጣና የዓለም የጂኦ-ፖለቲካ ፉክክር ማዕከል ሆኗል።
ቀይ ባሕር ዝም ብሎ የውኃ አካል አይደለም፤ የዓለም ኢኮኖሚ "የደም ሥር" ነው።
በቀን በሚሊዮን የሚቆጠር በርሜል ነዳጅ የሚተላለፍበት ስልታዊ በር የሆነውን ባብ-ኤል-መንደብ እና አፍሪካን፣ አውሮፓን እና እስያን የሚያገናኝ የንግድ ድልድይ የሆነውን ስዊዝ ካናልን መቆጣጠር ለሀገራት የደኅንነት ዋስትና እና የኃይል ሚዛን የበላይነት ማረጋገጫ ሆኗል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላት ታሪካዊ ቀጣይነት፣ የሕዝብ ቁጥር እና የዲፕሎማሲ ማዕከልነት የቀጣናው "ምሰሶ ሀገር" ያደርጋታል።
በመሆኑም ኃያላን በደጃችን ላይ ወታደራዊ መሠረት እየገነቡ ባለበት ሁኔታ፣ ኢትዮጵያ ተመልካች ብቻ ሆና መቆየት አትችልም።
በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው አለመረጋጋት እና በቀይ ባሕር ላይ እየታየ ያለው ውጥረት፣ ኢትዮጵያ አስተማማኝ የባሕር መዳረሻ እንዲኖራት እና የባሕር ኃይሏን እንድታጠናክር የሕልውና ግዴታ ጥሎባታል።
የኢትዮጵያ ጂኦ-ፖለቲካዊ ስኬት የሚረጋገጠው በውስጣዊ መረጋጋት እና ጠንካራ ኢኮኖሚ፣ በአርቆ አሳቢ ዲፕሎማሲ እና ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስቀድም አንድነት ነው።
ሀገራችን የራሷን የሕልውና መስመር በማበጀት፣ የቀጣናው የሰላም እና የንግድ ማዕከልነቷን በተግባር የምታረጋግጥበት ወቅት አሁን ነው።
የታሪካዊቷ ኢትዮጵያ ስልታዊ መነሣት በዝምታ የሚታለፍ ሳይሆን፣ የትውልድ አደራ እና የብሔራዊ ክብር ጉዳይ ነው!
ይህ ሐሳብ በሰፊው የተዳሰሰበትን መረጃ አስተያየት መስጫ ሳጥን ውስጥ ከተቀመጠው የድረ ገጻችን ሊንክ ያገኛሉ፦


AM

የሎጂስቲክና የተዋጊ መሀንዲሶች ተመረቁ…………
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም
የሰሜን ምስራቅ ዕዝ በስሩ ከሚገኙ ኮሮች እና ክፍለጦሮች አውጣጥቶ ያሰለጠናቸውን የሎጀስቲክ እና የተዋጊ መሀንዲስ ሙያተኞች አስመርቋል።
በአፍሪካ ከፍተኛ የሚባል የህዝብ ቁጥር ያላት ሀገር የባህር በር አልባ ሆና መቆየቷ ፍትሃዊ ያለመሆኑን የጠቀሱት ዋና አዛዡ መንግስት ላነሳው ፍትሃዊ ጥያቄ ጠንካራ ተፅዕኖ ፈጣሪ ኃይል መገንባት ያስፈልጋል ብለዋል።
የተዋጊውን ኃይል ግስጋሴ ማፋጠን እና የጠላትን እንቅስቃሴዎች በመሰናክል የመገደብን ጥበብ ሰልጣኞች በሚገባ መቅሰማቸውን የመሀንዲስ ስልጠና አስተባባሪ ሌተናል ኮሎኔል አብዱራህማን ሰማን ገልፀዋል።




AM

የኮንትሮባንድ ዕቃ የጫነ ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ
በአንድ ዲክላራሲዮን የገቡ ዕቃዎች ተከፋፍለው እንዲለቀቁ ሊፈቀድ ይችላል ተብሏል
የኮንትሮባንድ ዕቃ ጭኖ ሲጓዝ የተገኘ ተሽከርካሪ ይጣልበት የነበረውን አንድ መቶ ሺሕ ብር ቅጣት በመሻር፣ ሙሉ በሙሉ ተሸከርካሪው እንዲወረስ የሚያደርግ የጉምሩክ ረቂቅ ማሻሻያ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ፡፡
ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበውና ሪፖርተር የተመለከተው የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ሰነድ፣ በኮንትሮባንድ የተሰማሩ ተሽከርካሪዎች ባለቤቶች በወንጀሉ ተሳታፊ ባልሆኑበት ሁኔታ ንብረታቸው እንዲወረስ መደረጉ ፍትሐዊ አይደለም በሚል ምክንያት፣ በአዋጅ ቁጥር 1160/2011 አንቀጹ ተሻሽሎ፣ የተሽከርካሪው ባለቤት 100 ሺሕ ብር ብቻ እንዲቀጣ መደንገጉን ያስታውሳሉ።
ሆኖም የተሽከርካሪ ባለቤቶች የሚቀጡት የገንዘብ መጠን 100 ሺሕ ብር በመሆኑ ዕቃው ቢያዝም ኮንትሮባንዲስቱ ይህንን ገንዘብ ለመክፈል እንደሚስማማና ኮንትሮባንድ እንደሚያጧጥፍ መረጃዎች በመጠቆማቸው፣ ዕቃዎችን ለመደበቅ የሚያስችል አካል የተገጠመለት ሙሉ በሙሉ የኮንትሮባንድ ዕቃ ጭኖ ሲጓዝ የተገኘ ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚያስችል አንቀጽ በማሻሻያው ተካቷል።
በሥራ ላይ ያለው አዋጅ በአንድ ዲክላራሲዮን አገር ውስጥ የገቡ ዕቃዎች ተከፋፍለው ሊለቀቁ የሚችሉ መሆኑን ስለማይደነግግ፣ አስመጪዎች በገንዘብ እጥረት ምክንያት ለሁሉም ዕቃዎች ሊከፈል የሚገባውን ቀረጥ ከፍለው መረከብ በማይችሉበት ጊዜ ችግር ሲያጋጥማቸው እንደሚታይ ተጠቅሷል..
via ethiopianreporter.com

AM

ደቡብ ዕዝ የጽናት ቅኝት፣ የሐገራዊ ወኔ እና የአንድነት ተምሳሌት ነው
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም
ወታደራዊ ወኔ ዝም ብሎ የሚመጣ ስሜት አይደለም። በበረሃው ረመጥ፣ በጋራው ቁልቁለትና በፈታኝ ግዳጆች እቶን ውስጥ ተፈትኖ የሚወጣ የአሸናፊነት ማንነት እንጂ። የደቡብ ዕዝ ባለፉት ዐሥርተ ዓመታት በኢትዮጵያ ወታደራዊ ታሪክ መዝገብ ላይ የከተበው ዐቢይ ገጽ ቢኖር፣ ይህንኑ የማይበገር ዘላቂ የሆነ የሐገር ፍቅር ወኔ ነው። ዛሬ ይህ ዕዝ የዓመታት የክብር ጉዞውን ሲታሰብ፣ ዝም ብሎ የዓመታት ተከታታይነትን መቁጠር ሳይሆን፤ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በማይናወጥ ዐለት ላይ መቆሙን ማብሰር ነው።
የደቡብ ዕዝ የደረሰበት የጥንካሬ ማማ መሰረቱ፣ በዕውቀትና በልምድ የታነፀው ብርቱ መሪነቱ ነው። ዕዙ ራዕይን ወደ ተግባር የሚቀይሩ፣ በውጊያ ሜዳ የከረሙና በስትራቴጂ የታጠቁ ብርቅዬ መሪዎች ባለቤት ነው። እነዚህ መሪዎች ለሠራዊቱ መሪና አስተማሪ፣ ለጠላት ደግሞ የማይደፈር የብረት አጥር ናቸው።
የአመራሩ ጥበብና ቆራጥነት ሰራዊቱን እንደ አንድ የልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ አድርጎ አስተሳስሮታል። በፈታኝ ወቅት መረጋጋትን፣ በድል ጊዜ ደግሞ ትሕትናን የተላበሰው ይህ መሪነት፤ የዕዙ ስኬትና የኢትዮጵያ ኩራት ምንጭ ሆኖ ቀጥሏል።
1969 ዓ.ም ምስረታ ማለዳ ጀምሮ፣ የደቡብ ዕዝ ስም ከድልና ከጽናት ጋር የተቆራኘ ድርና ማግ ነው። በተለያዩ ግንባሮች የታየው ያ ተጋድሎ፣ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በነፃነት አድማስ ላይ ከፍ አድርጎ አቆይቷል። ይህ ወኔ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚጋባ፣ ከደም ጋር የሚዋሃድ የጀግንነት አደራ ነው። አንጋፋው መኮንን ለወጣቱ ሐገር ጠባቂ የሚያስተላልፈው ትልቁ ጥይትን ብቻ ሳይሆን፣ "ሐገር ካለች እኔ አለሁ" የሚለውን ጽኑና የማይበገር እምነት ነው።
የደቡብ ዕዝ ጥንካሬ በታሪክ ማህደር ብቻ የሚቀመጥ ሳይሆን፣ በወቅታዊው የሐገር ህልውና ዘመቻም እሳት ውስጥ አልፎ የነጠረ ነው። ዕዙ የሐገሪቱን ደህንነትና የሕዝቡን ሰላም ለማናጋት የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን በመመከት ረገድ የማይነቀነቅ ግንብ ሆኖ ቆሟል።
ድንበር ተሻጋሪውን የአሸባሪው አልሸባብ የጥፋት ሴራ በማምከን፣ በሐገር ውስጥ ሰላምን ለማደፍረስ የሚሞክሩትን የሸኔ የጥፋት ቡድኖችንና በጽንፈኝነት የታወረውን ኃይል እንቅስቃሴ በማርገብ ረገድ ዕዙ የጽናት ተምሳሌት ሆኗል። ሰላምን በጠመንጃ አፈሙዝ ለመቀማት የሚሹ ኃይሎች ሁሉ በደቡብ ዕዝ ፊት ተስፋቸው ሲከሽፍ ታይቷል።
በዕዙ ጥላ ስር የምናየው ሰራዊት የታላቋ ኢትዮጵያ ማሣያ ነው። በግዳጅ ቀጠናም ሆነ በማንኛውም ጊዜ ልባቸው አንድ ነው። ይህ የአንድነት መንፈስ ለዕዙ የማይበገር ጉልበትና የማይፈርስ ድልድይ ሆኖታል። በደቡብ ዕዝ መዝገበ ቃላት ውስጥ እኔ የሚል አግላይ ቃል የለም፤ ያለው "ኢትዮጵያ" የምትባል ታላቅ እናት ሀገር ብቻ ናት።
የደቡብ ዕዝ ተልዕኮ በጦር ሜዳ ውሎና በድንበር ጥበቃ ብቻ የታጠረ አይደለም፤ ይልቁንም የሕዝብ አለኝታነቱን በተግባር የገለጠበት የልማት አሻራው የጥንካሬው ሌላኛው ገጽታ ነው። ዕዙም በተለያዩ መርሆች በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ አረንጓዴ አሻራን በማኖር፣ የውኃና የጤና መሰረተ ልማቶችን በመገንባት እንዲሁም በተፈጥሮ አደጋ ወቅት የደረሰለት ፈጣን ደራሽ በመሆን የሕዝብ ልጅነቱን አስመስክሯል።
ሰራዊቱ ጠመንጃውን ለሰላም፣ ጉልበቱን ደግሞ ለልማት በማዋል ካለበት ቀጠና ሕዝብ ጋር የፈጠረው ስነ-ልቦናዊ ትስስር፤ ወታደራዊ ግዳጁን በታላቅ የሕዝብ ድጋፍ እንዲወጣ የብረት ምሰሶ ሆኖታል። ይህ የልማት ተሳትፎ ዕዙን ከሰላም ዘብነት ባለፈ፣ የሕዝብ የችግር ቀን ደራሽ አድርጎታል።
ዛሬ ደቡብ ዕዝ በታሪክ ትውስታ ብቻ የሚኖር ተቋም አይደለም። በቴክኖሎጂ የፈረጠመ፣ በሰው ኃይል የሰለጠነ እና ወቅታዊ የጸጥታ ስጋቶችን በብቃት መመከት የሚችል ኃይል ነው። የደህንነት መረጃዎችን እና የሰለጠነ የሰው ኃይልን በማቀናጀት የሐገሪቱን ደቡባዊ ድንበር እንደ አይን ብሌን ይጠብቃል።
ከደቡብ ዕዝ የሠራዊት ሥነ-ልቦና ግንባታ

AM
Daniel Daba retweetledi

ቅድሚያ ለሴቶች!
ሴቶች በጥበብ ይኖራሉ፤ በራስ መተማመን ይሠራሉ፤ በራስ መተማመን ይሮጣሉ፤ ይችላሉም! ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን የአገራችንን ብልፅግና እናረጋግጣለን።
ዛሬ ማለዳ 16 ሺህ ሴቶች የሚሳተፉበትን የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በድምቀት አስጀምረናል። በታላቁ ሩጫ አዘጋጅነት በየዓመቱ የሚካሄደው ይህ ውድድር፤ ዘንድሮ በኮሪደር ልማታችን አማካኝነት እጅግ ውብ፣ ምቹ እና ለከተማችን አዲስ ዘመናዊ መልክ ባላበሰው በቦሌ - አትላስ - ኡራኤል መንገድ ላይ በልዩ ድምቀት ተከናውኗል።
እንኳን ደስ አላችሁ!
ሁላችሁም አሸናፊዎች ናችሁ!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ክብርት ከንቲባ @AdanechAbiebie
AM

አርሶ/አርብቶ አደሩን ሜካናይዜሽን ማስታጠቅ የቅድሚያ ቅድሚያ ተግባራችን ነው።
ግብርና ሚንስቴር በተለያዩ ፕሮግራሞች፣ ፕሮጀክቶች እና አጋር አካላትን በማስተባበር በ2.3 ቢሊየን ብር ወጪ የተገዙ የግብርና ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋጥ የሚያግዙ የተለያዩ የሜካናይዜሽን መሳሪያዎች እና ተሽከሪካሪዎችን ለክልሎች በድጋፍ አስረክቧል።
ባዛሬው ዕለት ለክልሎች በድጋፍ የተላለፉት ማሽነሪዎች እና ተሽከርካሪዎች፣-
1. 63 ትራክተሮች (41 ትራክተሮች በATI ድጋፍ፣ 22 ትራክተሮች በኮሪያ መንግስት ድጋፍ የተገዙ)
2. 71 Walking ትራክተሮች ( በኮሪያ መንግስት ድጋፍ)
3. 150 የሩዝ መፈልፈያ ማሽኖች (በFSRP ድጋፍ)
4. 78ሺህ ጫጩቶችን በአንድ ጊዜ ማስፈልፈል የሚያስችሉ ባለ ብዙ ደረጃ አራት የዶሮ ጫጩት ማስፈልፈያዎች ( በFSRP ድጋፍ)
5. 5 የከርሰ ምድር ውሃ ማዉጫ ሪጎች ( በFSRP ድጋፍ)
6. 243 ያማሃ ሞተር ሳይክሎች ( 90 ያማሃ ሞተር ሳይክሎች በRLLP ድጋፍ፣ 153 ያማሃ ሞተር ሳይክሎች በበረሃ አንበጣ መከላከል ፕሮጀክት ድጋፍ)
7. 15 የመስክ ተሽከርካሪዎች ( በበረሃ አንበጣ መከላከል ፕሮጀክት ድጋፍ)
8. 460 የሶላር ፓምፖች ( በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ድጋፍ)
9. 980 ኮምፒዩተር እና እና የICT እቃዎች ( በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ድጋፍ ) የተገዙ ናቸው
10 5 የቡና ላቦራቶሪዊች ( በFSRP ድጋፍ የተገዙ)
ድጋፍ ያደረጉልንን የልማት አጋሮቻችን ከልብ እናመሰግናለን!




AM



