Sputnik Ethiopia

9.8K posts

Sputnik Ethiopia banner
Sputnik Ethiopia

Sputnik Ethiopia

@sputnik_ethio

🇪🇹 ትኩስ እና ልዩ የአፍሪካ መረጃዎች፣ ትንታኔዎች እና አስተያየቶች ስለ አፍሪካ በእንግሊዘኛ ቋንቋ፤ @sputnik_africa

Katılım Mart 2025
40 Takip Edilen4K Takipçiler
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
🏢 የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እስከ ሚያዚያ ወር መጨረሻ ድረስ በመዲናዋ ሁሉም ክፍለ ከተሞች እንደሚጀምር ተገለፀ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በልደታ ክፍለ ከተማ የተገነባውንና ሦስተኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል የአገልግሎት መስጫ ማዕከልን መርቀው ሥራ አስጀምረዋል። 📍ተጨማሪ ሦስት ማዕከላት በመጋቢት ወር ቀሪ ቀናት የሚከፈቱ መሆኑን የገለጹት ከንቲባዋ፤ እስከ ሚያዚያ መጨረሻ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እንደሚጀመር አስታውቀዋል። 👉 አዲስ መሶብ ዜጎች በአገልግሎት ምክንያት የሚደርስባቸውን እንግልት፣ የጊዜና የጉልበት ብክነት ከማስቀረት አንፃር መሠረታዊ ለውጥ እያስገኘ መሆኑን ከንቲባዋ ጠቅሰዋል።
Sputnik Ethiopia tweet media
AM
0
0
5
167
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
🚀 የሩሲያ ሮኬት ጭስ ሰማይ ላይ የፈጠረው ድንቅ ዕይታ 🇷🇺 ከባይኮኑር ኮስሞድሮም የተተኮሰው ሶዩዝ-2.1ኤ ሮኬት፤ በበርካታ የሩሲያ ግዛቶች ሊታይ የሚችል ደማቅ እና ማራኪ የጭስ መስመር በሰማይ ላይ ጥሎ አልፏል።
AM
0
0
1
129
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
‘ጳጳሱ’ ተብሎ የሚጠራውን ድመት ይተዋወቁ 🐱⛪️ በቤተ-ክርስቲያን መግቢያ ለምዕመናን ቡራኬ እየሰጥ የሚመስለውን “ኮኮ” የተባለ ድመት፤ የአካባቢው ነዋሪዎች “የቤተ-ክርስቲያኑ ጳጳስ” በማለት ይጠሩታል።
AM
0
1
7
444
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
📌 30 ሴኮንድ በስፑትኒክ አፍሪካ 👉 የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት አሁንም ተባብሶ እንደቀጠለ ነው፡፡ የኢራን ጦርነት የአፍሪካ አየር መንገዶች ላይ የደቀነውን ስጋት በ30 ሴኮንድ ቃኝተነዋል፡፡
AM
0
0
0
74
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
የኢትዮጵያ ባሕላዊ መድኃኒቶች ወደ ፋብሪካ ምርት ሊሸጋገሩ ነው ሀገሪቱ ለዘመናት ስትጠቀምባቸው የቆዩ 8 የባሕላዊ መድኃኒቶች በሳይንሳዊ መንገድ ተፈትሸው ለንግድ ምርት ዝግጁ መሆናቸውን የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት አስታውቋል። 🌿 ስምንቱ መድኃኒቶች ለባክቴሪያ፣ ለፈንገስ እና ለሌሎች የተለመዱ የጤና እክሎች መፍትሔ የሚሰጡ ሲሆን በቤተ ሙከራና በክሊኒካዊ ፍተሻዎች ደህንነታቸውና ፈዋሽነታቸው መረጋገጡን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል። 🔬መድኃኒቶቹ የምርምር ምዕራፋቸውን አጠናቅቀው ወደ ፋብሪካ ምርት የሚሸጋገሩበት ዝግጅት መገባደዱም ተጠቁሟል።
Sputnik Ethiopia tweet media
AM
0
5
17
656
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
አልጄሪያ እና ኒጀር አጋርነታቸውን ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ለመቀየር ዝግጁነታቸውን ገለፁ 🇩🇿🇳🇪 የአልጄሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲፊ ግሪብ ከኒጀር አቻቸው ዓሊ ማሃማን ላሚን ዜን ጋር የሁለቱን ሀገራት ከፍተኛ የጋራ ኮሚሽን ሁለተኛ ጉባኤ ሰኞ ዕለት በኒያሜ በሊቀመንበርነት መርተዋል። ሀገራቱ በጉባኤው ትብብራቸውን ይበልጥ ለማስፋት መስማማታቸውን ሚዲያዎች ዘግበዋል። 👉ቅድሚያ ለመስጠት የተስማሙባቸው ጉዳዮች፦ ◻️ እስካሁን የተመዘገቡ ስኬቶችን ማጠናከር፣ ◻️ ዋና ዋና የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ማፋጠን፣ ◻️ የኢኮኖሚ አጋርነትን ማሳደግ።
AM
0
0
1
55
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
"በኢትዮጵያውያን አትሌቶች ላይ የውጤት ማሳጣት ሴራ እየተፈጸመ ነው" - ጋዜጠኛ ቦጋለ አበበ 🇪🇹🏃‍♀️ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቪዛ ምክንያት በ21ኛው የቶሩን የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና አለመሳተፋቸው፤ የሀገሪቱን ስፖርታዊ የበላይነት ለመቀነስ የታቀደ "የውጤት ማሳጣት ተግባር" እንደሆነ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ምክትል ዋና አዘጋጅ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጿል። 🗣️ "የሆነ የውጤት ማሳጣት ሴራ እንደሚፈጸም ነው እኔ አሁን እየገባኝ ያለው... እንደ ኢትዮጵያ ያሉ የታዳጊ ሀገራት አትሌቶች በቪዛ ሂደት፣ በተለያዩ ፖለቲካዊ አንደምታ ባላቸው ጉዳዮች ምክንያት ቪዛ እያጡ ዕድላቸውን መጠቀም እየቻሉ አይደለም" ብሏል፡፡ 👉 ጋዜጠኛው ክልከላው ለኢትዮጵያም ሆነ ለአትሌቶች ትልቅ ጉዳት እንደሆነ አብራርቷል፡፡ 🗣️ "ኢትዮጵያ ትታወቅበት በነበረው የቤት ውስጥ የዓለም ሻምፒዮና ከ25 ዓመት በኋላ ምንም ዓይነት ሜዳሊያ ሳታገኝ እንድትመለስ ነው ያደረጋት። ይሄ እንደ ውጤት ትልቅ ቀውስ ነው፤ የሩብ ክፍለ ዘመን ታሪክ ተበላሸ ማለት ነው።"
Sputnik Ethiopia tweet media
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio

ፖላንድ የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ጽጌ ዱጉማንና ሦስት ኢትዮጵያውያን አትሌቶችን ቪዛ ከለከለች 🥈 በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ በሴቶች 800 ሜትር የብር ሜዳሊያ በማሸነፍ በታሪክ የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት እና ሌሎች የመካከለኛ ርቀት ሯጮች ሳሮን በርሄ፣ ሀረገወይን ካላዩ እና ሞሲሳ ስዩም በፖላንድ ቶሩን እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና እንዳይሳተፉ ታግደዋል። 🇵🇱🇺🇸 የፖላንድ የቪዛ እገዳ ባሳለፍነው ጥር ወር በፍሎሪዳ ታላሃሲ ተዘጋጅቶ በነበረው የዓለም አትሌቲክስ የታዳጊዎች ሻምፒዮና ውድድር 14 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ከተከለከሉ በኋላ የመጣ ነው፡፡ 🇪🇹 እነዚህ ክልከላዎች ኢትዮጵያ ሜዳሊያ የምታገኝባቸው ውድድሮች እንዲቀንሱ የሚያደርጉ እና "ስፖርታዊ አፓርታይድ" እንደሆኑ የዘርፉ ባለሙያዎች አሳስበዋል፡፡

AM
0
1
0
180
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
🇮🇷⚔️🇺🇸 በኢራን የሚደረግ የምድር ወረራ ለአሜሪካ የሰቆቃ ወራት ይሆናል - የቀድሞ መኮንን አሜሪካ የኻርግ ደሴትን ጨምሮ ወደ ኢራን ወታደሮቿን ከላከች ከፍተኛ ኪሳራ እንደሚደርስባትና ግጭቱን ለወራት አልፎ ተርፎም ለዓመታት ሊያራዝመው እንደሚችል ጡረተኛው የአሜሪካ ጦር ሌተናል ኮሎኔል ኧርል ራስሙሰን ለስፑትኒክ ገልጸዋል። 💬 "ይህ ማለት ወታደሮችን በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል መላክ ወይም በሌላኛው የፋርስ ባሕረ ሰላጤ አቅጣጫ በሳዑዲ አረቢያ በኩል ማሳረፍ ማለት ነው። ሁለቱም መንገዶች እጅግ አዳጋች ይሆናሉ" ሲሉ ተናግረዋል።
Sputnik Ethiopia tweet media
AM
0
0
1
249
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአፍሪካ በዓይነቱ የመጀመሪያውን ግዙፍ የጭነት አውሮፕላን ሊያስገባ ነው ✍🏼 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ከዓለም አቀፉ የአውሮፕላን ኪራይ ኩባንያ ኤርካፕ ጋር ሁለት ቦይንግ 777-300ኢአርኤስኤፍ የተሰኙ ግዙፍ የጭነት አውሮፕላኖችን ለመከራየት ስምምነት ተፈራርሟል። ✈️ አውሮፕላኑ በአሁን ሰዓት ካሉ ባለ ሁለት ሞተር የረጅም ርቀት የጭነት አውሮፕላኖች 25 በመቶ የበለጠ የመጫን አቅም ስላለው የአየር መንገዱን የጭነት አገልግሎት ቅልጥፍና በእጅጉ የሚያሳድግ ነው ተብሏል። 🔜 የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖቹን በፈረንጆቹ 2028 ሁለተኛ ሩብ ዓመት ይረከባል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
Sputnik Ethiopia tweet media
AM
0
7
66
3.3K
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
ናሚቢያ የኤለን መስክ የስታርሊንክ ሳተላይት የሥራ ፈቃድ እንዳያገኝ አገደች 🇳🇦👉 የናሚቢያ የኮሙዩኒኬሽን ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ውሳኔውን ያስተላለፈበትን ዝርዝር ምክንያት ባይገልጽም፤ በባለሥልጣኑ ተነሳሽነት ወይም በስታርሊንክ ጥያቄ በሚቀጥሉት 90 ቀናት ውስጥ እንደገና ሊታይ እንደሚችል መግለጹን አንድ የደቡብ አፍሪካ የዜና ወኪል ዘግቧል። እንደ ዘገባው ከሆነ፤ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣኑ በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም ስታርሊንክ ያለ ፈቃድ እየሠራ ነው በሚል አገልግሎቱን እንዲያቆም እና ሕገ-ወጥ የተባሉ የኩባንያው መሣሪያዎች እንዲወረሱ መመሪያ ሰጥቶ ነበር። 🇿🇦🇨🇲 ስታርሊንክ እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ካሜሩን ባሉ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ተመሳሳይ የሕግ መሰናክሎች እና ከመንግሥት የቴሌኮም ተቋማት ተቃውሞ እየገጠመው ይገኛል።
AM
0
1
3
488
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ለባለሀብቶች ካስተላለፈችው 2.3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ ጥቅም ላይ እየዋለ ያለው 45 በመቶ ብቻ ነው ተባለ 🚜 የግብርና ሚኒስቴር ከባለድርሻ አካላት ጋር ባካሄደው የምክክር መድረክ፤ በሀገሪቱ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የውጭ ምርት ጥገኝነትን ለመቀነስ የግል ባለሀብቱ ሚና ወሳኝ ቢሆንም የዘርፉ አፈጻጸም ግን አሁንም ፈታኝ ሆኖ መቀጠሉ ተገልጿል። 🗣 ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ለ8,742 ባለሀብቶች ከተላለፈው 2.3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ በንቁ ልማት ላይ የሚገኘው ከግማሽ በታች መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ 👉 ይህን ለማሻሻል ተግባራዊ የተደረገው አዲሱ የግብርና እና ገጠር ልማት ፖሊሲ ለኢንቨስትመንት ልዩ ትኩረት መስጠቱን ጠቅሰው ምርታማነትን ለማሳደግ ከፍተኛ ርብርብ እንደሚጠይቅ ገልፀዋል።
AM
0
0
0
167
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
🇿🇼 ዚምባብዌ የኢራን ጦርነት የፈጠረውን ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመቋቋም የመከላከያ እርምጃዎችን እየወሰደች እንደምትገኝ ገለጸች 🗣️ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋጓ የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ከፈጠረው ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ዚምባብዌን ለመጠበቅ መንግሥታቸው እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ገልጸዋል። 👉 የሀራሬ መንግሥት ዜጎችን ከጦርነቱ የኢኮኖሚ ተፅዕኖ ለመታደግ እንደ የታክስ እና የደመወዝ ክለሳ ያሉ ጣልቃ ገብነቶችን ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
Sputnik Ethiopia tweet media
AM
1
0
3
444
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
🇪🇹 ኢትዮጵያ የናይል ወንዝ የቀጣናው ሀገራት የቤተሰባዊ ትስስርና የጋራ ብልጽግና ምንጭ እንዲሆን ያላትን ጽኑ አቋም ዳግም አረጋገጠች የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ፤ ግድቡ ለሱዳንና ግብፅ የጎርፍ መከላከልና የተስተካከለ የውሃ ፍሰት እንዲኖር የሚያደርግና ለቀጣናዊ የኤሌክትሪክ ትስስር የሚውል እንጂ ስጋት አለመሆኑን አረጋግጠዋል። 🗣️ "ውሃን ከፖለቲካ ነፃ በማድረግ በሳይንሳዊ መረጃዎች ላይ የተመሠረተ ትብብር መፍጠር ለሁሉም ሀገራት ተጠቃሚነት ወሳኝ ነው" ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ 💧 ሚኒስትሩ አክለውም በኢትዮጵያ ከፍተኛ ስፍራዎች ላይ የውሃና አካባቢ ጥበቃ ካልተደረገ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የውሃ ህልውና አደጋ ላይ እንደሚወድቅ በማስጠንቀቅ፤ የተፋሰሱ ሀገራት እንደ ድርቅና ጎርፍ ባሉ የጋራ ተግዳሮቶች ላይ በጋራ መሥራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
AM
0
0
3
180
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
በቴል አቪቭ ንጋቱን በተሰነዘረ የአየር ጥቃት ስድስት ሰዎች ቆሰሉ 🇮🇱 በአየር ጥቃቱ አንድ ባለ አራት ፎቅ መኖሪያ ሕንፃ ላይ ውድመት እንደደረሰና በአቅራቢያው እሳት መቀስቀሱን የእስራኤል መገናኛ ብዙኃን ዘገቧል። 🇮🇷 ከኢራን የተተኮሰው ሚሳኤል በሦስት ወይም በአራት ንዑስ ጥይቶች የሚከፋፈል እና እያንዳንዳቸው 100 ኪሎ ግራም የሚመዝኑ ፍንጣሪዎችን የያዘ የጦር ራስ እንደነበረው ተገልጿል።
AM
0
1
0
205
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
“ዩክሬን በሳኅል ቀጣና አለመረጋጋት ውስጥ የመሠሪ ሚና እየተጫወተች ነው” - ተንታኝ ባቲዮኖ ሀሳኔ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ በዳካር የዩክሬን አምባሳደር “ለአሸባሪ ቡድን ድጋፍ ማድረጋቸውን በይፋ መናገራቸውን” አስታውሰዋል። 🗣 ማሊ ጦር ላይ ጥቅም ላይ ከዋሉት አጥፍቶ ጠፊ ድሮኖች መካከል አንዳንዶቹ “በእርግጥም ከዩክሬን የመጡ ናቸው” ሲሉ የቡርኪና ፋሶው የፖለቲካ ተንታኝ ገልጸዋል። በቡርኪና ፋሶ፣ በማሊ እና በኒጀር ተፅዕኗቸው የተመናመነባቸው የምዕራባውያን ሀገራት “አሸባሪ ቡድኖችን ለማስታጠቅ ዩክሬንን እንደ መሳሪያ ይጠቀማሉ።” 📽️ ተንቀሳቃሽ ምሥሉ የማሊ ጦር በየካቲት ወር በያንፎሊላ በአሸባሪዎች ላይ የሰነዘረው ጥቃት ያስከተለውን ውጤት ያሳያል።
AM
0
0
2
123
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
❗️ሩሲያ እና የአፍሪካ አጋሮቿ ለሦስተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ እየተዘጋጁ ነው - ሰርጌ ላቭሮቭ ሦስተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ጉባኤ በ2026 ሁለተኛ አጋማሽ እንደሚካሄድ መገለፁ የሚታወስ ነው።
AM
0
1
5
340
Sputnik Ethiopia
Sputnik Ethiopia@sputnik_ethio·
አፍሪካን ያላካተተ ዓለም አቀፍ መድረክ ከዚህ ወዲህ ተቀባይነት አይኖረውም - የሕግ መምህር 🇺🇳 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አሁን ያለውን የዓለም ነባራዊ ሁኔታ እንዲያንጸባርቅ አስቸኳይ መዋቅራዊ ለውጥ ያስፈልገዋል ሲሉ የአርሲ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር ጃራ ሳሙኤል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። 🗣️ “ተመድ የተመሠረተው ከ70-80 ዓመታት በፊት በነበረ እውነታ ላይ በመሆኑ፤ አሁን ያለውን የዓለም ኃይል ሚዛን አይወክልም። አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ ሊኖራት ይገባል” ብለዋል። 👉 መምህሩ አክለውም የጸጥታው ምክር ቤት በአፍሪካ ጉዳይ ሌሎች የሚወስኑበት መድረክ መሆኑ ማብቃት እንዳለበት አስረድተዋል። 🗣️ “አሁን በተለይ ታላላቅ ሀገራት አፍሪካን በተመለከተ ያላቸው አመለካከት በፊት እንደነበረው አይደለም። አሁን ላይ አፍሪካ ቁልፍ ሚና እንደምትጫወት ሁሉም እያወቀው የመጣበት ጊዜ ነው።"
Sputnik Ethiopia tweet media
AM
0
0
5
574